Entries by Mahibere Kidusan

‹‹የጥበብ መጀመሪያ እግዚአብሔርን መፍራት ነው፤ ሰነፎች ግን ጥበብንና ተግሣጽን ይንቃሉ›› (ምሳ. ፩፥፯)

‹‹እግዚአብሔርን መፍራት ለጥበብ ዘውድዋ ነው›› እንደተባለ ከእግዚአብሔር የሆነው ጥበብ መጀመሪያው እርሱን መፍራት ነው፤ (ሲራክ ፩፥፲፰)፡፡ እግዚአብሔርን መፍራት ስንል በቁጣው ይቀሥፈኛል፣ በኃያልነቱ ያጠፋኛል ከሚል የሥጋትና የጭንቀት መንፈስ ሳይሆን የዓለሙ ፈጣሪና መጋቢ እርሱ መሆኑን በማመን በፈቃዱ መገዛትና መኖር ማለታችን ነው፡፡

በዓታ ለማርያም

ቅድስት ድንግል ማርያም በ፶፻፬፻፹፭ ዓመተ ዓለም ከሐና እና ከኢያቄም በፈቃደ እግዚአብሔር ተወልዳ እስከ ሦስት ዓመት ድረስ የኖረችው በወላጆቿ ቤት ነበር፡፡ ከዚህ በኋላ ኢያቄምና ሐና የተሳሉትን ስእለታቸውን አስታውሰው ወስደው ለቤተ እግዚአብሔር ሰጧት፤

‹‹የእውነት መንፈስ በመጣ ጊዜ ወደ እውነት ሁሉ ይመራችኋል›› (ዮሐ.፲፮፥፲፫)

ይህች ዓለም ከእውነት የራቀች መኖሪያዋን በሐሰት መንደር ያደረገች መሆኗ ይታወቃል፡፡ ሰው ማንነቱን አጥቶ በበደል ምክንያት በሐሰት ኖሯል፡፡ ሰው በፈቃዱ ጥፋት ምክንያት ከሚፈጽማቸው በደሎች ትልቁ በደል ውሸት ነው፡፡ ውሸት ተሸንፎ ይወድቃል፤ ከሕይወት ይርቃል፡፡ የኀጣአን ሁሉ ራስ ሐሰት ናት፡፡ ክፋትን ከራሱ አንቅቶ የበደለ ዲያብሎስ አቡሃ ለሐሰት፤ የሐሰት አባት የተባለው ለዚህ ነው (ዮሐ.፰፥፵፬)፡፡

ሥርዓተ ንባብ

ውድ አንባብያን በባለፉት ትምህርታችን ስምና የስም ዓይነቶች በሚል ርእስ በተከታታይ ማቅረባችን ይታወሳል፤ በዛሬውና በሚቀጥሉት ተካታታይ ትምህርታችን ደግሞ ስለ ንባብ ምንነት፣ ዓይነትና ስልት እንመለከታለን፤ መልካም ንባብ!

የመካነ ነገሥት ግምጃ ቤት ማርያም የሐዲስ ኪዳን ደቀ መዛሙርት ተመረቁ

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን በማእከላዊ ጎንደር ሀገረ ስብከት በመካነ ነገሥት ግምጃ ቤት ማርያም የመጻሕፍተ ሐዲሳት እና ሊቃውንት ጉባኤ ቤት 18 የሐዲስ ኪዳን ደቀ መዛሙርት ኅዳር 21 ቀን 2012 ዓ.ም ሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያን እና ሕዝበ ክርስቲያን በተገኙበት በታላቅ ድምቀት ተመረቁ፡፡

ታቦተ ጽዮን

ታቦተ ጽዮን በእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ትመሰላለች፤ ይህን ለመረዳት ስለ ታቦተ ጽዮን አሠራርና መንፈሳዊ ትርጉም አስቀድመን ልናውቅ ይገባናል፡፡

የኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ሃይማኖት ተከታይ የሆኑ የዩኒቨርስቲ ተማሪዎች ግፍ እየተፈጸመባቸው መሆኑ ተገለጸ

በአለፉት ሳምንታት የኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ሃይማኖት ተከታይ ተማሪዎችን ከሚማሩበት ዩኒቨርስቲዎችና ኮሌጆች በማሳደድ እና የተወሰኑትን እንዳይወጡ በማገድ ሙሉ በሙሉ ከትምህርት ማፈናቀል የጀመሩት የጥፋት ኃይሎች በመቱና ቦንጋም ተመሳሳይ ድርጊት እየፈጸሙ መሆኑ ተገለጸ፡፡

ጾመ ነቢያት

ጾመ ነቢያት ምንም እንኳን ዓላማው አንድ ቢሆንም የተለያዩ ስያሜዎች አሉት፡፡ በዋነኝነት ነቢያት ስለጌታ ሰው መሆንና ስለ ሰው መዳን የጸለዩትን ጸሎት የጾሙትን ጾም በማሰብ፤ የአምላክ ሰው መሆንን ምሥጢር በትንቢት ተመልክተው ለእኛ ለሰው ልጆች የሚከፍለውን የፍቅር ዋጋ አስበው ጾመውታልና ጾመ ነቢያት ይባላል፡