በዓታ ለማርያም
ንጽሕተ ንጹሐን፣ ቅድስተ ቅዱሳን፣ ከተመረጡ የተመረጠች፣ ከተለዩ የተለየች፣ ከተከበሩ የተከበረች እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ቤተ መቅደስ የገባችበት ታኅሣሥ ፫ ቀን ‹‹በዓታ ለማርያም›› በቅድስት ቤተ ክርስቲያናችን በድምቀት ይከበራል፡፡
This author has not written his bio yet.
But we are proud to say that Mahibere Kidusan contributed 1043 entries already.
ንጽሕተ ንጹሐን፣ ቅድስተ ቅዱሳን፣ ከተመረጡ የተመረጠች፣ ከተለዩ የተለየች፣ ከተከበሩ የተከበረች እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ቤተ መቅደስ የገባችበት ታኅሣሥ ፫ ቀን ‹‹በዓታ ለማርያም›› በቅድስት ቤተ ክርስቲያናችን በድምቀት ይከበራል፡፡
ጥበብ ከእግዚአብሔር አምላክ የሚሰጥ፣ ከሁሉ የበለጠና የላቀ የዕውቀት ሥጦታ እንዲሁም ሰማያዊ ርስትን የሚያወርስ መንፈሳዊ ጸጋ ነው፡፡ በሰዎች አእምሮ ውስጥም ማስተዋልን ያጎናጽፋል፡፡ በዚህም ጸጋ የእውነት መንገድን ማወቅና ጽድቅን መሥራት ይቻላል፡፡ ጠቢቡ ሰሎሞን በምሳሌው እንደተናገረው ‹‹ለጠቢብ ሰው ትምህርትን ስጠው፤ ጥበብንም ያበዛል፤ ጽድቅንም አስተምረው ዕውቀትን ያበዛል፡፡›› (ምሳ. ፱፥፱)
ውድ የእግዚአብሔር ልጆች! ለተከበረው ጤንነታችሁ እንደምን አላችሁ? ነቢየ እግዚአብሔር ንገሥ ክቡር ዳዊት በመዝሙሩ ‹‹… እግዚአብሔር ሕፃናትን ይጠብቃል…›› በማለት እንደተናገረው በእግዚአብሔር ጥበቃ በሰላምና በጤና እንደቆያችሁልን ተስፋችን የታመነ ነው፡፡ (መዝ.፻፲፬፥፮)
ውድ አንባብያን! እንደምን ሰነበታችሁ? ባለፈው ትምህርታችን የግሥ ዝርዝር በዐሥሩ መራሕያን ዓይተን ነበር፡፡ በዚህም ክፍለ ጊዜያችን ለሰጠናችሁ መልመጃ ምላሽና ስሞችን በመራሕያን እንዴት መዘርዘር እንደምችል አዘጋጅተን አቅርበንላችኋል፡፡ መልካም የትምህርት ክፍለ ጊዜ ይሁንላችሁ!
በተከበረች በኅዳር ፳፮ ቀን ንዑድ ክቡር ንጹሕ መነኰስ ኢትዮጵያዊ ጻድቅ አባታችን አቡነ ሀብተ ማርያም የዕረፍቱ መታሰቢያ ነው። ይህም ቅዱስ አባት የትውልድ ሀገሩ የራውዕይ በምትባል በስተ ምሥራቅ ባለች ሀገር ውስጥ ሲሆን በዚያም ስሙ ፍሬ ቡሩክ የሚባል አንድ ደግ ሰው ነበረ። ይህም ከክቡራን ሰዎች ወገን የሆነ ሰው እጅግ ሀብታምም የነበረ ሲሆን በሕጋዊ ጋብቻ ያጋቡት ቡርክት የሆነች ስሟ ዮስቴና የምትባል ሚስት ነበረችው። እርሷም በበጎ ምግባርና ሥራ የተጌጠች ናት። ይህችውም ደግ እናታችን በሕግ ተወስና ሳለች በጽኑዕ ገድል፣ በጾም በጸሎት በምጽዋትና በስገድትም ትጋደል ነበር።…
የቅዱስ መርቆሬዎስም ወላጆች አስቀድመው አረማውያን ነበሩና የክርስትና ጥምቀትን በጸጋ ተቀበሉ፤ አባቱንኖህ እናቱንም ታቦት ብለው ሰየሟቸው፤ ቀድሞ ፒሉፓዴር የነበረውም ስሙ ተለውጦ መርቆሬዎስ ተባለ፡፡ ‹መርቆሬዎስ› ማለትም የአብ ወዳጅ ማለት ነው፤ ዳግመኛም የኢየሱስ ክርስቶስ አገልጋይ ማለት ነው፡፡ የውሻ መልክ ያላቸው ግን መልአኩ በተገለጠላቸው ጊዜ እንደነገራቸው ለቅዱስ መርቆሬዎስ አባት የሚታዘዙና የሚያገለግሉ ሆኑ፡፡
ያች ያማረ ወርቅን የተጫማች
እንደአጥቢያ ጨረቃ ብርሃን የተመላች
ለክረምቱ ስደት መጠለያ ሆነች
ጽዮንን ክበቧት ሰማይ ታደርሳለች!
በዓለም የምናያቸው መልካምም ሆኑ ክፉ ነገሮች ሁሉ መነሻቸው ሐሳብ መሆኑን ስናስተውል ኅሊና ምን ያህል ታላቅ መሆኑን እንገነዘባለን፡፡ ኅሊና የሚለው ቃል ‹ሐሳብ፣ ምኞት፣ ከልብ የሚመነጭ ሐሳብ› ማለት ነውና፡፡ በሰው ልጆችም የአእምሮ ሥራ ሂደት ውስጥ ሐሳብ ሲደጋገም ወደ አመለካከት፣ ከሐሳብ የተነሣ አመለካከት ሲያድግም ክፉ ወይም በጎ ወደ ሆነ ማመን፣ አንድ ሰው ከሐሳቡ ወደ ማመኑ የደረሰበት መንገድም ማንነቱን እንደሚወስኑት ባለሙያዎች ያስተምሩናል፡፡ ከሐሳባችን ተነሥቶ ወደ ማንነታችን የደረሰ ነገርም ፍጻሜያችንን ይወስነዋል፡፡…
ከሰባቱ የአዋጅ አጽዋማት መካከል አንዱ የሆነውን ጾመ ነቢያት በየዓመቱ ከኅዳር ፲፭ ጀምሮ እስከ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የልደት በዓል ድረስ በአምላካችን ቅዱስ ፈቃዱ እንጾማለን!
የተወደዳችሁ የእግዚአብሔር ልጆች! እንደምን ሰነበታችሁ? እግዚአብሔር ይመስገን አላችሁ? መልካም፤ እግዚአብሔር አምላካችን የተመሰገነ ይሁን፡፡ ባላችሁበት ሆናችሁ ትምህርታችሁን በጥሞና ተከታተሉ!
ልጆች! ለዛሬ ይዘንላችሁ የቀረብነው ትምህርት ስለ ጾም ነው፡፡ በመጀመሪያ ጾም ምን ማለት እንደሆነ እና እናንተ ሕፃናት ከሰባት ዓመት ዕድሜያችሁ ጀምሮ እንዴት መጾም እንዳለባችሁ እናስተምራችኋለን፡፡
