በዓለ ልደቱ ለአቡነ አረጋዊ
የጻድቁ የአቡነ አረጋዊ አባት ይስሐቅ እናቱም እድና ይባላሉ፡፡ ሁለቱም እግዚአብሔርን የሚፈሩና የሚያከብሩ ነበሩ፡፡ እግዚአብሔር አምላክም የተባረከውን ልጅ ሰጣቸው፤ይህም የሆነው በጥር ፲፬ ቀን ነው፡፡
This author has not written his bio yet.
But we are proud to say that Mahibere Kidusan contributed 977 entries already.
የጻድቁ የአቡነ አረጋዊ አባት ይስሐቅ እናቱም እድና ይባላሉ፡፡ ሁለቱም እግዚአብሔርን የሚፈሩና የሚያከብሩ ነበሩ፡፡ እግዚአብሔር አምላክም የተባረከውን ልጅ ሰጣቸው፤ይህም የሆነው በጥር ፲፬ ቀን ነው፡፡
የተወደዳችሁ አንባብያን! እንደምን ሰነበታችሁ? የእግዚአብሔር አምላካችን ስም የተመሰገነ ይሁን! ባለፈው የትምህርታችን ክፍለ ጊዜ ስምንቱን የግሥ አርእስት አስተምረናችሁ ነበር፡፡ በዚህ ሳምንት ደግሞ ለሰጠናችሁ መልመጃ ምላሽና አምስቱ አዕማድን እንመለከታለን፤ በጥሞና ተከታተሉን!
ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከእናቱ ከቅድስተ ቅዱሳን ድንግል ማርያም እና ከቅዱሳን ሐዋርያቱ ጋር በመሆን በገሊላ አውራጃ በቃና መንደር በሠርግ ቤት ተገኝቶ ቤተ ከብካቡን በትምህርቱ በተአምራቱ ባረከ።በጥምቀት በዓል ማግስት ጥር ፲፪ ቀን ይህንኑ ጠብቀን በዓሉን እናከብራለን፡፡
ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ዮርዳኖስን ብርህት ማኅፀን እንድትሆን፣ ምእመናንም ከአብራከ መንፈስ ቅዱስ፣ ከማኅፀነ ዮርዳኖስ ዳግም ተወልደው መንግሥተ ሰማያት እንዲገቡ እንደዚሁም ሥርዓተ ጥምቀትን ለማስተማርና አብነት ለመሆን በጥር ዐሥራ አንድ ቀን ተጠምቋልና ይህችን የተከበረች ቀን ሕዝበ ክርስቲያን ያከብር ዘንድ ይገባል፡፡
የተከበራችሁ የእግዚአብሔር ልጆች! እንዴት አላችሁ? እንኳን ለብርሃነ ጥምቀቱ አደረሳችሁ! ልጆች! የጌታችንን የልደት በዓልን እንዴት አሳለፋችሁ? በሰላም እንዳሳለፋችሁ ተስፋችን ነው፤ ትምህርትስ እንዴት ነው? የግማሽ መንፈቀ ዓመት ፈተናም እየደረሰ ነውና በርትታችሁ አጥኑ!
ውድ የእግዚአብሔር ልጆች! ዛሬ ደግሞ ስለ ጥምቀት በዓል እንማማራለን፡፡ ጥምቀት ማለት ‹‹አጥመቀ- አጠመቀ›› ከሚለው የግእዝ ግስ የወጣ ሲሆን ‹‹መነከር፣ መድፈቅ፣ በተባረከው ውኃ ጸበል ውስጥ ሦስት ጊዜ ብቅ ጥልቅ›› ማለት ነው፤ እንግዲህ በዛሬ ትምህርታችን ስለ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ጥምቀት እንመለከታለን፡፡
አጋእዝተ ዓለም ሥላሴ በኃጢአት የተገነባውን የሰናዖር ግንብ ያፈረሱበት አንድነታቸውንና ሦስትነታቸውን በግልጽ ያሳዩበት ጥር ሰባት ቀን የከበረ በዓል እንደመሆኑ በቤተ ክርስቲያናችን በድምቀት ይከበራል፡፡ታሪኩ በኦሪት ዘፍጥረት ላይ እንደተጻፈ እንዲህ ይነበባል፡፡…
ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ወደ ቤተ ግዝረት በመግባት የኦሪት ሕግ የሆነውን ግዝረት የፈጸመበት ዕለት ጥር ስድስት ቀን በቤተ ክርስቲያናችን ይከበራል፡፡ ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ ‹‹ጌታ ክርስቶስ በሥጋ ግዝረትን ተቀበለ፣ ለአባቶች የተሰጠውን ቃልኪዳን ይፈጽም ዘንድ›› ብሎ መስክሯል፡፡ (ሮሜ ፲፭፥፰)
በትዳር ሕይወት ስንኖር ባል ራስ ነውና ሚስቶች ለባሎቻቸው እንዲገዙና እንዲታዘዙ ሲያዛቸው፣ ለባሎች የሰጠው ትእዛዝ ደግሞ ከዚህ የጸና ትእዛዝ ነው። ይኸውም የገዛ ሕይወቱን አሳልፎ እስኪሰጥላት ድረስ ጌታችን አምላካችን እና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ቅድስት ቤተ ክርስቲያንን እንደወደዳት ባልም እንዲሁ ሚስቱን እንዲወዳት ጽኑዕ ትእዛዝን አዟል። ታዲያ ከመታዘዝና ከመገዛት ይልቅ ምን ያህል የሚጸና እንደሆነ ልናስተውለው ይገባል።
ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ለቤተ ክርስቲያን በፍቅር ሞቷል እና ቤተ ክርስቲያን ለክርስቶስ ትገዛለች፤ በተመሳሳይ ፍቅር ምክንያት ‹‹ሚስቶች ሆይ፤ ለጌታ እንደምትገዙ ለባሎቻችሁም ተገዙ፤ ክርስቶስ አካሉ ለሆነችው ቤተ ክርስቲያን ራስዋ እንደሆነ ሁሉ፣ አዳኝዋም እንደ ሆነ ወንድ ለሴት ራስዋ ነውና፡፡
ኢየሩሳሌም ከተማ ከወትሮው በተለየ መልኩ የፍርሃት ድባብ ተንጸባርቆባታል፤ በንጉሥ ሄሮድስ ቤተ መንግሥት ዙሪያ በሠራዊቱና በቤተ መንግሥቱ የቅርብ ሰዎች የሰሞኑ ወሬ የሦስቱ ነገሥታት ጉዳይ ነው፡፡ ከሩቅ ምሥራቅ ሠራዊቶቻቸውን አስከትለው የመጡት ማንቱሲማር፣ በዲዳስፋ፣ እና ሜልኩ የተባሉ ነገሥታት በእስራኤል ምድር መምጣታቸው ብቻ ሳይሆን ተወልዷል ለተባለው ንጉሥ እጅ መንሻ ለመስጠት እንደመጡ መናገራቸው ንጉሥ ሄሮድስን ቅር አሰኝቶታል፤ ፍርሃት በልቡ እንዲነግሥም አድርጎታል፡፡…