መስቀሉን ስከተል
ሊሄድ በ’ኔ መንገድ
ሊከተለኝ ‘ሚወድ
ራሱን ለሚክድ
አይደንግጥ አይፍራ
አለሁ ከር’ሱ ጋራ
This author has not written his bio yet.
But we are proud to say that Mahibere Kidusan contributed 1023 entries already.
ሊሄድ በ’ኔ መንገድ
ሊከተለኝ ‘ሚወድ
ራሱን ለሚክድ
አይደንግጥ አይፍራ
አለሁ ከር’ሱ ጋራ
ሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያን ምድር በገነት ወይም በሲኦል ልትመሰል እንደምትችል ያስረዳሉ፡፡ በቤተ ክርስቲያን ወርቃማ ዘመናት ተብሎ የሚጠሩትንም በመጥቀስ የተመረጡ ቅዱሳን ነገሥታት የነገሡበት፣ ደጋግ አባቶች የኖሩበት፣ ሊቀ ጳጳሳትና ጳጳሳት እንዲሁም ቀሳውስትና ካህናት በበጎና በመልካም መንገድ ምእመናንን መርተው በቅድስና ሕይወት ለርስተ መንግሥተ ሰማያት ባበቁበት ጊዜ ምድር በገነት ትመሰል እንደነበር ያስረዳሉ፡፡
በሀገረ አንጾኪያ ከአሕዛብ ወገን የተለወደው አይሁዳዊው ሉቃስ ከሰባ ሁለቱ አርድእት የተቆጠረ ባለ መድኃኒትና ወንጌልን የጻፈ ቅዱስ ሐዋርያ ነው፡፡ ሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያን በወንጌል ትርጓሜያቸው ስሙ ‹ዓቃቤ ሥራይ› ወይም ‹ባለ መድኃኒት› የሚል ትርጉም በውስጡ የያዘ መሆኑን ያስረዳሉ፡፡ በላቲን ቋንቋ ‹ሉካስ› ማለት ‹ብርሃናማ፣ ብርሃን የያዘ› ማለት ነው፡፡ መጽሐፈ ስንክሳር ደግሞ ብልህና ጥበበኛ በማለት ይገልጸዋል፡፡
በዐሥራ ስምንት ዓመት ዕድሜው የመነኮሰ፣ ትዕግሥቱ እጅግ የበዛ እንዲሁም የመታዘዝ ጸጋ የተሰጠው ቅዱስ አባታችን ዮሐንስ ሐጺር የዕረፍት መታሰቢያ ጥቅምት ሃያ ቀን ነው፡፡ ሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያን እንደሚገልጹትም ይህ ጻድቅ ከቅዱሳን አባቶች መካከል በቁመት እንደ እርሱ አጭር ስላልነበረ ‹‹ቅዱስ ዮሐንስ ሐጺር፤ አጭሩ አባ ዮሐንስ›› ተብሏል፡፡ የእርሱን ቁመትና የቅድስና ሕይወቱን ሲያነጻጽሩም ‹‹ቁመቱ እጅግ ያጠረ ጽድቁ ግን ከሰማይ የደረሰ ቅዱስ ዮሐንስን ሰላም ሰላም እንለዋለን›› በማለት ተናግረዋል፡፡
ውድ የእግዚአብሔር ልጆች እንዴት አላችሁልን? ትምህርት እንዴት ነው? መቼም በክረምቱ የዕረፍት ጊዜያችሁ ትምህርት እስኪከፈት በጣም ጓጉታችሁ እንደነበር እናስባለን! ይኸው ተከፈተላችሁ! እንግዲህ በርትታችሁ ከአሁኑ መማር፣ ማጥናት፣ የቤት ሥራን መሥራት፣ ያልገባችሁን መጠየቅ ይገባችኋል፡፡ ገና ነው እያላችሁ እንዳትዘናጉ ጥናቱን አሁኑኑ ጀምሩ! የጨዋታም ሆነ ቴሌቪዥን የምታዩበት ጊዜ ከትምህርታችሁ ጋር በማይጋጭ መልኩ መሆን አለበት፡፡ ከሁሉም ትምህርታችሁን አስቀድሙ! ውድ እግዚአብሔር ልጆች! ለዛሬ ያዘጋጀንላችሁ የሊቀ ዲያቆናትና የቀዳሜ ሰማዕት ቅዱስ እስጢፋኖስን ታሪክ ነው፡፡
የተወደዳችሁ አንባብያን! እንደምን ሰነበታችሁ? የእግዚአብሔር አምላካችን ስም የተመሰገነ ይሁን! የጥቅምት ወር የመጀመሪያ ክፍለ ጊዜያችን ወደ ሆነው ትምህርት ከመግባታችን በፊት ስለ ባለፈው ጥቂት እናስታውሳችሁ፡፡ ከዘመን መለወጫ ጋር ተያይዞ ለንግግር የሚጠቅሙንን የመግባቢያ ዓረፍተ ነገሮችና የንግግር ስልቶች አቅርበንላችሁ ነበር፡፡ ይህም ለእናንተ የንግግር ክህሎት በሚረዳ መልኩ አዘጋጅተን ያቀረብንላችሁ በ፳፻፲፬ ዓመተ ምሕረት በድረ ገጹ በቀረቡት ትምህርቶች የተማራችኋቸውን ቃላትም ሆነ ግሦች በመጠቀም እንድትለማመዷቸው በማሰብ ነው፤ ይህንን ተግባራዊ እንዳደረጋችሁትም ተስፋችን ነው፡፡
ታስታውሱ እንደሆነ ያለፈው ዓመት የመጨረሻ ትምህርታችን ስለ ነገረ ግሥና አገባብ ነበር፤ እንደሚታወቀው ዓረፍተ ነገሮችን ለመሥራት የሚጠቅሙን ከስሞች ቀጥሎ በዋነኛነት ግሦች በመሆናቸው በእነርሱ ላይ የበለጠ ትኩረት አድርገን በዚህ ሳምንት ያቀረብንላችሁ ትምህርት ከግሥ ዓይነቶች አንዱ ስለሆነው ‹ረብሐ› ግሥ ነው፡፡
በሥነ ፍጥረት መጀመሪያ ቀን ‹‹ብርሃን ይሁን›› በማለት የተናገረው አምላካችን ልዑል እግዚአብሔር ነው፡፡ (ዘፍ.፩፥፫) ‹‹ብርሃን ይሁን›› በማለት በተናገረ ጊዜም ጨለማ ተገፈፈ፡፡ መጽሐፈ ሥነ ፍጥረት እንደሚነግረን ቅዱሳን መላእክትም ይህ ብርሃን ዕውቀት ሆኗቸው አምላካቸው እግዚአብሔርን ‹‹ቅዱስ ቅዱስ ቅዱስ›› በማለት በአዲስ ምስጋና አመሰገኑት፡፡ ‹‹እኔ ፈጣሪያችሁ ነኝ›› ያለ የሰይጣን ክህደትም በብርሃኑ ተጋለጠ፡፡ (ሊቀ መዘምራን ሞገስ ዕቁበ ጊዮርጊስ መጽሐፈ ሥነ ፍጥረት)
በዓለመ ሰማይ እግዚአብሔር አምላክ ፍጥረቱን መፍጠር በጀመረበት በመጀመሪያው ቀን እሑድ አስቀድሞ የተፈጠሩት ሰባቱ ሰማያትና መላእክት ናቸው፡፡ ሰማያቱም እንደ ስያሜያቸው የራሳቸው ትርጓሜ አላቸው፡፡
ልቤ ተነሣስቶ ጽድቅህን ፍለጋ
ከማዳንህ ጋራ አንተኑ ሊጠጋ
ልሂድ ወደ ዱሩ ከአባቶች ማደሪያ
ከለምለሙ መስክህ ከጽድቅ መነኻርያ
