Entries by Mahibere Kidusan

ከጥምቀት በኋላ ክርስትና

ውድ የእግዚአብሔር ልጆች! እንዴት አላችሁ? የጥምቀት በዓል እንዴት አለፈ? እናንተስ የጥምቀትን በዓል እንዴት አከበራችሁት? ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ለእኛ አብነት ለመሆን እንዲሁም ደግሞ የዕዳ ደብዳቤያችንን ሊደመስስልን መጠመቁን ምክንያት በማድረግ በየዓመቱ በደስታ በምስጋና በዓሉን እናከብራለን፡፡ መቼም ልጆች! ከወላጆች አልያም ከጓደኞቻችን ጋር በመሆን አክብራችኋል፤ መልካም!

ሌላው ደግሞ ወቅቱ ለእናንተ ለተማሪዎች የዓመቱ አጋማሽ የምዘና ፈተና ነበር! ፈተናስ እንዴት ነበር? እንግዲህ የዓመቱ አጋማሽ የትምህርት ወቅት አልቆ ፈተናም ተፈትናችሁ ውጤት የተሰጣችሁ እንዲሁም ውጤት በመጠባበቅ ላይ ያላችሁ ትኖራላች፡፡ ከባለፈው ውጤታችሁ በመነሣት በቀጣዩ የትምህርት ጊዜ በርትታችሁ ለመማር እንደ ምታቅዱ ተስፋችን እሙን ነው፡፡ ደግሞ በዕረፍት ጊዜያችሁ መልካምን ነገር በማድረግ አሳለፉ፡፡ በርቱ! ለዛሬ የምንነግራችሁ ከጥምቀት በኋላ ክርስትና ምን ይመስላል የሚለውን እንመለከታለን፤ መልካም ቆይታ!

“እንስሳትን ጠይቅ ያስተምሩህማል፤ የሰማይ ወፎችን ጠይቅ ይነግሩህማል” (ኢዮብ ፲፪፥፯)

በጻድቁ ኢዮብ መጽሐፍ የተጻፈ ኃይለ ቃል ነው፡፡ አምላካችን ልዑል እግዚአብሔር በዕለተ ሐሙስ “ውኃ ሕያው ነፍስ ያላቸውን ተንቀሳቃሾች ታስገኝ” በማለት ቃል በተናገረ ጊዜ በልባቸው የሚሳቡ፣ በእግራቸው የሚሽከረከሩ፣ በክንፋቸው የሚበሩ ፍጥረታት ከባሕር ተገኙ፡፡ (ዘፍ.፩፥፳)

በባሕር ከተፈጠሩ ከነዚህ ፍጥረታት የሚበሉና የሚገዙ፣ የማይበሉ የማይገዙም አሉ፡፡ ከባሕር ጸንተው የሚኖሩ አሉ፤ አንድ ጊዜ በየብስ አንድ ጊዜ በባሕር የሚኖሩ አሉ፤ በክንፋቸው በረው ከባሕር ወጥተው የቀሩም አሉ፡፡ (መጽሐፈ ሥነፍጥረት ምስለ አምስቱ አእማደ ምሥጢር፤ ገጽ ፷፤ ሥነ ፍጥረት ክፍል ሦስት ለከፍተኛ የመንፈሳዊ ትምህርት ተማሪዎች የተዘጋጀ ገጽ ፵)

በዓለ ዕረፍታ ለማርያም

እንኳን ለእናታችን ለቅድስተ ድንግል ማርያም በዓለ ዕረፍት በሰላም አደረሳችሁ!

የቅድስት ድንግል ማርያም ሞት ግን ይደንቃል! የሞትን ኃይል ያጠፋ፣ ሞትን በሞቱ የገደለ፣ ክርስቶስን ወልዳ ሳለ መሞቷ ይደንቃል። እናም “ለምን ሞተች?” ብሎ መጠየቅ የተገባ ነው፤ ይኸውም በተአምረ ማርያም ተጽፎ እንደምናገኘው በሲኦል ያሉ ነፍሳትን አሳይቷት ስለነበር በልጇ ሞት ነፍሳት እንደዳኑ በእርሷ ሞትም ነፍሳትን እንደሚያድንላት ስለነገራት ስለ ኃጢአተኞች ነፍሷን በልጇ ትእዛዝ ሰጠች።

“ክፉውን በመልካም አሸንፍ እንጂ በክፉ አታሸነፍ” (ሮሜ ፲፪፥፳፩)

ክፉና በጎ የሰው ልጆች ባሕርያት ናቸው፡፡ ይሁን እንጂ እግዚአብሔር ዓለምን ሲፈጥር ለመልካም ነበረ፡፡ (ዘፍ.፩፥፲፪) ምንም እንኳን የፍጥረት አክሊል የሆነው ሰው ነጻ ፈቃዱን ተጠቅሞ ከብርሃን ጨለማን፣ ከሕይወት ሞትን፣ ከመታዘዝ አለመታዘዝን ቢመርጥም እግዚአብሔር አምላክ የፈጠረው ስሙን እንዲቀድስ ክብሩን እንዲወርስ ነበረ፡፡ ለዚህም ክፉና ደጉን መለየት ይችል ዘንድ አስቀድሞ የሚያስተውል አእምሮ ሰጥቶት ነበር፡፡ በኅሊናው መመራት ተስኖት የሰው ልጅ ከወደቀ በኋላ ዳግመኛ የተጻፈ ሕግ ሰጥቶታል፡፡ ሰዎች ራሳቸው ላይ የክፉ ብድራት እንዳይደርስባቸው አስበው በባልንጀራቸው ላይ ክፉ እንዳያደርጉ ክፉ ላደረጉ የክፉ ብድራት እንዲከፈላቸው ሙሴ ሕግን ጻፈላቸው፡፡

ቃና ዘገሊላ

ቅድስት ቤተ ክርስቲያናችን በጥር ፲፪ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በቃና ዘገሊላ በተደረገ ሠርግ ቤት ያደረገውን ተአምር በማሰብ በዓልን ታደርጋለች፡፡ ጌታችን ከጥምቀቱ በኋላ በዶኪማስ ሠርግ ቤተ ከእናቱ ቅድስት ድንግል ማርያም እንዲሁም ከደቀ መዛሙርቱ ጋር ታጋብዞ በነበረበት ጊዜ ለእንግዶች ወይን ጠጅ አለቀባቸው፡፡

‹‹በዮሐንስ ሊጠመቅ ከገሊላ ወደ ዮርዳኖስ መጣ›› (ማቴ.፫፥፲፫)

ውድ የእግዚአብሔር ልጆች! እንዴት አላችሁ! እንኳን አደረሳችሁ! የጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ልደት በዓል እንዴት አለፈ? ልጆች! አሁን ያላችሁበት ወቅት የዓመቱ አጋማሽ የፈተና ወቅት ነው! ፈተናውን በደንብ አድርጋችሁ መሥራት አለባችሁ! መቼም በርተታችሁ ስታጠኑና ያልገባችሁን ስትጠይቁ ስለነበር በፈተና የሚቀርቡላችሁን ጥያቄዎች በትክክል እንደምትመልሱ አንጠራጠርም! ምክንያቱም የምትጠየቁት የተማራችሁትን ስለሆነ በአንዳች ነገር እንዳትዘናጉ!

ታዲያ ልጆች! ፈተናውን የምትሠሩት ጥሩ ማርክ ለማምጣት ብቻ ሳይሆን ለእውቀትም መሆን አለበት፡፡ ዕውቀት ማለት በተግባር መተርም መሆኑን እንዳትዘነጉ! መልካም! ልጆች ዛሬ ስለ ጌታችንን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ጥምቀት እንማራለን፡፡

ሥርዓተ አምልኮ

በዓላት ከማንኛውም ቀናት የበለጠ አምላካችን እግዚአብሔርን የምናመሰገንባቸውና የምናወድስባቸው፣ የተቀደሱትን ዕለታት በማሰብና በመዘከር በዝማሬ፣ በሽብሻቦና በእልልታ የምናከብርባቸው ናቸው፡፡ ታቦታት ከመንበረ ክብራቸው የሚወጡባቸውና ሕዝበ ክርስቲያኑን የሚባርኩባቸው ስለሆኑም በክብርና በድምቀት ይከበራሉ፡፡