Entries by Mahibere Kidusan

‹‹ዑራኤል የተባለ መላእክ ሊረዳኝ መጣ›› (ዕዝ.ሱቱ ፪፥፩)

በመከራ ጊዜ ረዳት የሆነው የመላእክት አለቃ ቅዱስ ዑራኤል በዘመናት ለነገሡ የሀገራችን ነገሥታት ያደረገው ውለታ እጅግ ብዙ ነው፡፡ ዳግማዊ ቆስጠንጢኖስ የተባለ ንዋየ ማርያም በነገሠበት ዘመነ መንግሥት ቅዱስ ዑራኤል በጸሎቱ በመራዳትና እስከ ግዛቱ ፍጻሜ ባለመለየት ሀገሩን እንዲመራ አድርጓል፡፡…

ሕፃኑ ቅዱስ ቂርቆስና እናቱ ቅድስት ኢየሉጣ

ውድ የእግዚአብሔር ልጆች! እንዴት አላችሁልን? እንኳን ለወርኃ ክረምቱ አደረሳችሁ! በእግዚአብሔር ቸርነት፣ የተዘራው እህል በቅሎ ምድር ድርቀቷ ተወግዶ በአረንጓዴ ለምለም የምታጌጥበት ወቅት ነው፡፡ ለምድር ዝናምን ሰጥቶ፣ በዝናብ አብቅሎ፣ በነፋስ አሳድጎና በፀሐይ አብስሎ ፍጥረታቱን የሚመግብ የእግዚአብሔር ቸርነቱን እያወሳን ለምስጋና የምንተጋበት ወቅት ነው፡፡ በዚህ የዕረፍት ጊዜያችን ለቀጣይ የትምህርት ዘመን እየተዘጋጀን ወደ ቤተ እግዚአብሔር በመሄድ በርትተን፣ ውለታውን እያሰብን ለጸሎት ለቅዳሴ መትጋት አለብን!

ውድ የእግዚአብሔር ልጆች! ለዛሬ ያዘጋጀንላችሁ የሕፃኑ ቅዱስ ቂርቆስንና የእናቱ ቅድስት ኢየሉጣን ታሪክ ነው፡፡

ሶርያዊው ቅዱስ ኤፍሬም

ሜሶፖታሚያ በምትገኝ ንጽቢን ከተማ ከዋክብትን ከሚያመልኩ ሰዎች መካከል በ፫፻፮ ዓ.ም ገደማ የተወለደው ሶርያዊው ቅዱስ ኤፍሬም አባቱ ክርስትናን የሚጠላ ሰው እንደነበር ይነገራል፡፡ እንዲያውም ካህነ ጣዖት ስለመሆኑ መጽሐፈ ስንክሳር ይጠቅሳል፡፡ (ስንክሳር ሐምሌ ፲፭)

እርባ ቅምር

የተወደዳችሁ አንባብያን! እንደምን ሰነበታችሁ? የእግዚአብሔር አምላካችን ስም የተመሰገነ ይሁን! ባለፈው የትምህርታችን ክፍለ ጊዜ ‹‹እርባ ቅምር›› በሚል ርእስ የመጀመሪያውን ክፍል ይዘንላችሁ ቀርበን ነበር፡፡ በዚህ ሳምንት ደግሞ ለሰጠናችሁ መልመጃ ምላሽና ክፍል ሁለትን እናቀርብላችኋለን፤ በጥሞና ተከታተሉን!

ሰብእ

ለሰው ሰውነቱ
ከአፈር መስማማቱ
የሸክላ ብርታቱ
እሳት ነው ጉልበቱ
ውኃ ደም ግባቱ
ነበር መድኃኒቱ!

ዕረፍተ አባ ኪሮስ

በሀገረ ሮም ከአባቱ ንጉሥ አብያ ከእናቱ አንሰራ ተወለደ፡፡ ደጋግና ቅዱሳን ወላጆቹም እግዚአብሔርን በመፍራት እየኖሩበት በነበረበት ወቅት ይህን የተመረጠ አባት ሰጣቸው፤ አባ ኪሮስ የተወለደው በታኅሣሥ ፰ ቀን ነበር፡፡ ጻድቁ አባት በቅድስና ሕይወትና ትጋት ማዕረግ አባ ኪሮስ ከመባሉ በፊት ‹ዲላሶር› ተብሎ ይጠራ እንደነበር ታሪኩ ይገልጻል፡፡

አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ

‹‹ኮከበ ክብር ጽዱል ፀሐዬ አግዓዚ ብሩህ አቡነ ጊዮርጊስ ጥዑመ ስመ ወሠናየ ግዕዝ መጋቤ  ሃይማኖት ወመሠረተ ቤተ ክርስቲያን፤ አባታችን ጊዮርጊስ ዘጋስጫ የሚያበራ የክብር ኮከብ፣ የኢትዮጵያ ብሩህ ፀሐይ፣ ስሙ የሚጣፍጥ፣ ምግባሩ የቀና ነው።›› (ገድለ አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ)

ዘመነ ክረምት

የቀናት፣ የወራት እንዲሁም የዓመታት መገለጫዎች የሆኑት ወቅቶች በዘመናት ዑደት በመፈራረቅ በሚከሰቱበት የተፈጥሮ ሂደት ውስጥ ከሰዎች ሕይወት ጋር የጠበቀ ግንኙነት አላቸው፡፡ በብዙ መልኩም ተምሳሌትነታቸው የተገለጸ ነው፡፡ የሰው ልጅ በአበባ ይወለዳል፤ በንፋስ ያድጋል፤ በፀሐይ ይበስላል፤ በውኃ ታጥቦ ይወሰዳል፤ ይህም ምሳሌው በእግዚአብሔር ፍቃድ እንደምንወለድ፣ በክርስቲያናዊ ሕይወትም መከራና ሥቃይ እንደምንቀበል፣ እንድምንጸድቅና በሞት ወደ ዘለዓለም ዕረፍት እንደምንገባ ነው፡፡     

አሁን ያለንበት ወቅት ‹ዘመነ ክረምት› ከሞት በኃላ ሕይወት እንዳለ ሁሉ ከድካም በኋላ ዕረፍት እንዳለ የምናረጋግጥበት ወቅት ነው፤ መብረቅ፣ ነጎድጓድ፣ ባሕር፣ አፍላጋትና ጠል ጎልተው የሚታዩበት እና ፍሬዎች የሚታዩበት ዘመነ መስቀል ይገለጥበታል።

ሁለቱ የቤተ ክርስቲያን አዕማዶች

ቅዱሳኑ ሐዋርያት ጴጥሮስና ጳውሎስ የእግዚአብሔርን ቃል ለዓለም የሰበኩ፣ ብዙዎችን በክርስትና ጥምቀትና በገቢረ ተአምራት ያዳኑ የቤተ ክርስቲያን አዕማዶች ናቸው፡፡