Entries by Mahibere Kidusan

ታማኝነት

ውድ የእግዚአብሔር ልጆች! እንዴት አላችሁ? ታላቁ ዐቢይ ጾም እንዴት ነው? እንደ አቅማችሁ እየጾማቸችሁ ነው? የወላጆቻችሁ ድካማቸውና ክፍያቸው እናንተ ጎበዝ፣ ብልህ፣ አስተዋይና፣ ታማኝ ስትሆኑ ማየት ነውና በርቱ! ልጆች! ለዛሬ የምንማማረው ባለፈው የጀመርነውን ትምህርት የክርስቲያናዊ ሥነ ምግባር ቀጣዩን ክፍል “ታማኝነት” በሚል ርእስ ይሆናል፤ መልካም ቆይታ!

ዜና ዕረፍት

የብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርክ ልዩ ጽሕፈት ቤት እና የውጪ ግንኙነት መምሪያ የበላይ ኃላፊ እንዲሁም የድሬዳዋና የጅቡቲ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ ዶ/ር አቡነ አረጋዊ ከዚህ ዓለም ድካም ዐርፈዋል። ብፁዕነታቸው ለረጅም ጊዜ በሀገር ውስጥና ከሀገር ውጪ በሕክምና ሲረዱ ቆይተው ሊሻላቸው ባለመቻሉ ከዚህ ዓለም በሞተ ሥጋ ተለይተዋል።

በመንግሥትህ አስበኝ!

በሚያስፈራ ግርማህ በምጽዓት ቀን ስትገለጥ

በፊትህ የሚቆም ጠፍቶ ዓለም ሁሉ ሲንቀጠቀጥ

መልካሙን ዘር ከክፉው አበጥረህ ስትለያቸው

በፍርሃት ያርዳል የጽድቅ ፍሬ ለሌላቸው

ለእኔም ጨንቆኛል ዳግም የምትመጣበት

በደሌ ተቆጥሮ በሥራዬ የምመዘንበት

ዝክረ ግማደ መስቀሉ!

በአራተኛው መቶ ክፍለ ዘመን (በ፫፻፳፯ ዓ.ም) የንጉሥ ቆስጠንጢኖስ እናት ቅድት እሌኒ መስቀሉን ለማግኘት ወደ ኢየሩሳሌም ሄደች፡፡ ቅድት ዕሌኒ መስከረም ዐሥራ ስድስት ቀን በታሪክ አዋቂው አረጋዊው ኪራኮስ አማካኝነት ዕጣን እንዲጤስ አድረጋ በዕጣኑም ጢስ አመልካችነት መስቀሉን ከተቀበረበት ቦታ ለማውጣት በመስከረም ፲፯ ቀን ቍፋሮ አስጀምራለች፡፡ ንግሥት እሌኒ ከመስከረም ፲፯ ቀን አስጀምራ እስከ መጋቢት ፲ ቀን ሌሊትና ቀን ለሰባት ወራት ያህል የጉድፍን ኮረብታ ቆፍረው ቆሻሻውንም ካስወገዱ በኋላ ሦስት መስቀሎች ተገኙ፡፡ የጌታም መስቀል ሙት በማስነሣቱ ተለይቶ ታውቋል፡፡ መስቀሉ የተገኘው መጋቢት ፲ ቀን ፫፻፳፮ ዓ.ም. ነበር፡፡ በተመሳሳይ መልኩ መስቀሉ ከተቀበረበት ተራራ ተቈፍሮ የወጣበት መጋቢት ፲ ቀንም በቤተ ክርስቲያን በደማቅ ሥርዓት ይከበራል፡፡ በተጨማሪም መስከረም ፲፯ ቀን ንግሥት ዕሌኒ ቅዳሴ ቤቱን ያከበረችበትን የመታሰቢያ በዓል ታቦት አውጥተው ዑደት በማድረግ በቤተ ክርስቲያን ያከብሩታል፡፡ ከሦስቱ መስቀሎች መካከል ጌታችን የተሰቀለበት መስቀል የተለየው ተአምራት በማድረጉና ብዙ ድውያንን በመፈወሱ ነው፡፡

የበረሓው ኮከብ

በሕግ በሥርዓቱ ተጉዘው፣ ተጋድሏቸውን ፈጽመው፣ ዓለምን ንቀው፣ ከኃጢአት ሥራ ርቀው፣ በጽቅ ሥራ ደምቀው፣ የባሕሪው ቅድስናውን በጸጋ ተቀብለው፣ በቤቱና በቅጽሩ መታሰቢያ ከሰጣቸው አባቶቻችንን መካከል አንዱ ርእሰ ባሕታዊ ጻድቁ አባታችን አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ አንዱ ናቸው፡፡

ዜና ዕረፍት

ብፁዕ አቡነ ባስልዮስ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን በኒውዮርክ ሀገረ ስብከት የሮቸስተር ቅድስት ኪዳነ ምሕረት ገዳም የበላይ ጠባቂ ሊቀ ጳጳስ ከዚህ ዓለም ድካም ማረፋቸው ተገልጿል።ዕረፍታቸውንም ተከትሎ የቅዱስ ሲኖዶስ ጽሕፈት ቤት ያደረሰን መረጃ እንደሚያመለክተው ክቡር አስከሬናቸው በሚቀጥለው ሳምንት ቅዳሜ መጋቢት ፱/፳፻፲፭ ዓ/ም ወደ አዲስ አበባ የሚመጣ ሲሆን የቀብር ሥነ ሥርዓቱም በመንበረ ጸባዖት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል እንደሚፈጸም አስታውቋል።

ዜና ዕረፍት

የዝዋይ ሐመረ ብርሃን ቅዱስ ገብርኤል ገዳም አበምኔት ታላቁ የጸሎት አባት የኔታ መምህር ሐረገ ወይን ምሕረቱ በእርግና ምክንያት በ፺፱ ዓመታቸው መጋቢት ፩ ቀን ፳፻፲፭ ዓ.ም ከዚህ ዓለም ድካም ዐርፈዋል።ሥርዓተ ቀብራቸውም ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት፣ የጠቅላይ ቤተ ክህነት የመምሪያ ኃላፊዎች፣ የመንግሥት ባለሥልጣናትና ወዳጅ ዘመዶቻቸው በተገኙበት በዝዋይ ሐመረ ብርሃን ቅዱስ ገብርኤል ገዳም ተፈጽሟል።

የኔታ ሐረገ ወይን በርካታ ጳጳሳትንና ሊቃውንትን አስተምረው ያበቁ የአቋቋሙ ሊቅ ነበሩ። ከአርባ ዓመት በላይ ወንበር ዘርግተው ያስተማሩ፣ ከብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ተክለ ሃይማኖት ጊዜ ጀምሮ ሁለት ጊዜ ያክል ለጵጵስና ቢጠየቁም “ምንኩስናዬ ይበቃኛል” በማለት በዓታቸውን ያጸኑ ጸሎተኛ አባት እንደነበሩም ተገልጿል።

“ልትድን ትወዳለህ?” (ዮሐ.፭፥፭)

ቅድስት ቤተ ክርስቲያናችን የዐቢይ ጾም ሳምንታትን በቅዱስ ያሬድ ስያሜ መሠረት አራተኛውን ሳምንት መጻጉዕ ብላ ታከብራለች። “መፃጉዕ” ማለት “ድውይ፥ በሕመም የሚሰቃይ፥ የአልጋ ቁራኛ” ማለት ነው። ይህንንም ስያሜ እንዴት እንደመጣ ለማየት በዕለቱ የሚነበበውን የወንጌል ክፍል ብንመለከት እንዲህ ይላል። “ከታመመ ሠላሳ ስምንት ዓመት የሆነው አንድ ሰው ነበረ፤ ኢየሱስ ይህን ሰው ተኝቶ ባየ ጊዜ፥ እስከ አሁን ብዙ ዘመን እንዲሁ እንደ ነበረ አውቆ ‘ልትድን ትወዳለህ’ አለው። ድውዩም ጌታ ሆይ አዎን! ውኃው በተናወጠ ጊዜ በመጠመቂያይቱ ውስጥ የሚያኖረኝ ሰው የለኝም እንጂ፤ ነገር ግን እኔ በመጣሁ ጊዜ ሌላው ቀድሞኝ ይወርዳል አለ። ጌታ ኢየሱስም ‘ተነሣና አልጋህን ተሸክመህ ሂድ’ አለው። ወዲያውም ሰውዬው ዳነ፤ አልጋውንም ተሸክሞ ሄደ፤ ያም ቀን ሰንበት ነበረ” ይላል። (ዮሐ.፭፥፭-፲)

ክርስቲያናዊ ሥነ ምግባር

ውድ የእግዚአብሔር ልጆች! እንዴት ሰነበታችሁ? ትምህርት እንዴት ነው? መቼም ከመጀመሪያው የዓመቱ አጋማሽ ትምህርት ውጤታችሁ በመነሣት የበለጠ ጎበዝ ለመሆን እየተማራችሁ እንደሆነ ተስፋ እናደርጋለን! “ብልህ ልጅ ከስሕተቱ ይማራል” እንዲሉ አበው ከትናንት ድክመታችሁ በመማር የበለጠ ውጤታማ ተማሪ ለመሆን መሥራት ይገባል፡፡ ወላጆቻችን እኛን ለማስተማር ምን ያህል ዋጋ እንደሚከፍሉ አስተውሉ! ልጆች የእነርሱ ድካም እኛ መልካምና ጎበዝ እንድንሆን ነውና በርቱ! ለዛሬ የምንማማረው ስለ ክርስቲያናዊ ሥነ ምግባር ነው፤ መልካም ቆይታ!