ዐራቱ የእግዚአብሔር ሠራዊት

‹‹በእግዚአብሔር ዘንድ ዐራት ሠራዊት አየሁ፡፡ ሰባቱ ነጎድጓድ በተናገሩ ጊዜ ልጽፍ አሰብሁ፤ ከሰማይም ‹ሰባቱ ነጎድጓድ የተናገሩትን ነገር በማኅተም ዝጋው፤ አትጻፈውም› የሚል ድምጽ ሰማሁ››፤…

በዓለ ሢመቱ ለሊቀ መላእክት ቅዱስ ዑራኤል

ሊቀ መላእክት ቅዱስ ዑራኤል ከሰባቱ ሊቃነ መላእክት አንዱ በመሆን ከፍጥረተ ዓለም ጀምሮ በመብረቅና በነጎድጓድ ላይ በጥር ፳፪ ቀን የተሾመ መልአክ ነው፡፡ በመጽሐፈ ሄኖክ እንደተገለጸው መባርቅት ለጥጋብና ለበረከት እንዲበርቁ ነጎድጓድም ለሰላም እንዲሆን ያሠማራል፡፡ ለነቢዩ ሄኖክም የሰማይን ምሥጢርና ሰማያዊውን ዕውቀት ሁሉ የገለጸለት፤ የፀሐይን፣ የጨረቃን፣ የከዋክብትንና የሰማይ ሠራዊትን ብርሃንን የሚመራው ይኸው ገናና መልአክ ነው፡፡ (ሄኖ.፳፰፥፲፫)

‹‹የቅድስት ማርያም ሞት ግን ሁሉን ያስደንቃል›› ቅዱስ ያሬድ

ሊቁ ቅዱስ ያሬድ ‹‹ሞትሰ ለመዋቲ ይደሉ ሞታ ለማርያም የዐጽብ ለኵሉ፤ ሞት ለማናቸውም ሰው ሁሉ የተገባ ነው፤ የቅድስት ማርያም ሞት ግን ሁሉን ያስደንቃል›› በማለት የመሠከረው ስለ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ዕረፍት ነው፡፡ እርሷ በምድር ላይ በአይሁድ ክፋት ብዙ መከራና ኃዘን ካሳለፈች በኋላ በዘመነ ሉቃስ፣ ጥር ሃያ አንድ ቀን፣ በዕለተ እሑድ፣ በስድሳ ዐራት ዓመቷ ወደ ዘለዓለም ደስታ ትገባ ዘንድ ዐርፋለችና፡፡ (ጾመ ድጓ)

ዝርወተ አጽሙ ለቅዱስ ጊዮርጊስ

…ከዚህም በኋላ ቅዱሱን ወስደው በጐድጓዳ ብረት ምጣድ ውስጥ አበሰሉት፡፡ አቃጥለው አሳርረውም ሥጋውንና ዐጥንቱን ፈጭተው አመድ አድርገው ከረጅም ተራራ ላይ በተኑት፡፡ ይህም የሆነው ጥር ፲፰ ቀን ነው፡፡…

ዕረፍተ ሕፃን ቂርቆስ ወቅድስት ኢየሉጣ

በሮም ግዛት በሚገኝ አንጌቤን በሚባል ሀገር በፈሪሃ እግዚአብሔር፣ በክርስትና ሃይማኖት እና በበጎ ምግባር ጸንታ ትኖር የነበረች ኢየሉጣ የተባለች ደግ ሴት ነበርች፡፡ እርሷም ቂርቆስ የተባለ በሥርዓት ያሳደገችው ሕፃን ልጅ ነበራት፡፡ በዚያን ዘመን እለእስክንድሮስን የተበላ አረማዊ መኰንን  ነበር፤ ይህችም ቅደስት ከልጇ ጋር ከሮም ወደ ጠርሴስ ተሰደደች፡፡…

በዓለ ልደቱ ለአቡነ አረጋዊ

የጻድቁ የአቡነ አረጋዊ አባት ይስሐቅ እናቱም እድና ይባላሉ፡፡ ሁለቱም እግዚአብሔርን የሚፈሩና የሚያከብሩ ነበሩ፡፡ እግዚአብሔር አምላክም የተባረከውን ልጅ ሰጣቸው፤ይህም የሆነው በጥር ፲፬ ቀን ነው፡፡

አዕማድ

የተወደዳችሁ አንባብያን! እንደምን ሰነበታችሁ? የእግዚአብሔር አምላካችን ስም የተመሰገነ ይሁን! ባለፈው የትምህርታችን ክፍለ ጊዜ ስምንቱን የግሥ አርእስት አስተምረናችሁ ነበር፡፡ በዚህ ሳምንት ደግሞ ለሰጠናችሁ መልመጃ ምላሽና አምስቱ አዕማድን እንመለከታለን፤ በጥሞና ተከታተሉን!

‹‹በገሊላ አውራጃ በቃና መንደር ሠርግ ሆነ፤ ውኃውንም ወደ ወይንነት ለወጠው›› (ዮሐ. ፪፥፩-፲፩)

ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከእናቱ ከቅድስተ ቅዱሳን ድንግል ማርያም እና ከቅዱሳን ሐዋርያቱ ጋር በመሆን በገሊላ አውራጃ በቃና መንደር በሠርግ ቤት ተገኝቶ ቤተ ከብካቡን በትምህርቱ በተአምራቱ ባረከ።በጥምቀት በዓል ማግስት ጥር ፲፪ ቀን ይህንኑ ጠብቀን በዓሉን እናከብራለን፡፡

ጥምቀት

ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ዮርዳኖስን ብርህት ማኅፀን እንድትሆን፣ ምእመናንም ከአብራከ መንፈስ ቅዱስ፣ ከማኅፀነ ዮርዳኖስ ዳግም ተወልደው መንግሥተ ሰማያት እንዲገቡ  እንደዚሁም ሥርዓተ ጥምቀትን ለማስተማርና አብነት ለመሆን በጥር ዐሥራ አንድ ቀን ተጠምቋልና ይህችን የተከበረች ቀን ሕዝበ ክርስቲያን ያከብር ዘንድ ይገባል፡፡

በዓለ ጥምቀት

የተከበራችሁ የእግዚአብሔር ልጆች! እንዴት አላችሁ? እንኳን ለብርሃነ ጥምቀቱ አደረሳችሁ! ልጆች! የጌታችንን የልደት በዓልን እንዴት አሳለፋችሁ? በሰላም እንዳሳለፋችሁ ተስፋችን ነው፤ ትምህርትስ እንዴት ነው? የግማሽ መንፈቀ ዓመት ፈተናም እየደረሰ ነውና በርትታችሁ አጥኑ!

ውድ የእግዚአብሔር ልጆች! ዛሬ ደግሞ ስለ ጥምቀት በዓል እንማማራለን፡፡ ጥምቀት ማለት ‹‹አጥመቀ- አጠመቀ›› ከሚለው የግእዝ ግስ የወጣ ሲሆን ‹‹መነከር፣ መድፈቅ፣ በተባረከው ውኃ ጸበል ውስጥ ሦስት ጊዜ ብቅ ጥልቅ›› ማለት ነው፤ እንግዲህ በዛሬ ትምህርታችን ስለ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ጥምቀት እንመለከታለን፡፡