በዓለ ጰራቅሊጦስ

በዓለ ጰራቅሊጦስ የሚከበረው ርደተ መንፈስ ቅዱስን መሠረት በማድረግ በመሆኑ ምክንያት ጸጋ መንፈስ ቅዱስ ለመቀበል ነው፤ በዕለቱም ኢየሩሳሌም በተባለችው ቤተክርስቲያን ስለመጽናት፤ ከግለኝነት ይልቅ መንፈሳዊ አንድነትን ስለማስቀደም እና ስለመጸለይ  እንማራለን፡፡  

ግስ

ግስ ከቃል ክፍሎች አንዱ ሲሆን በብዙ መንገድ ሊፈታ ይችላል። በዋናነት ግን ድርጊት አመልካች የሆነ በዐረፍተ ነገር ውስጥ የሐሳብ መደምደሚያ፣ ወይም የዐረፍተ ነገር ማሠሪያ ተብሎ ይተረጎማል። በርካታ ምሁራን በተለያየ መልኩ ስላብራሩት የምሁራኑን አገላለጽ እንደሚከተለው እንመልከት።

የኢየሱስ ክርስቶስ ደም ከኀጢአታችን ሁሉ ያነጻናል፡፡ (፩ኛ ዮሐ.፩፥፯)

የሰው ልጅ ንስሓ ገብቶ ከኀጢአት ነጽቶ ቅዱስ ቊርባንን የሚቀበል ከሆነ ዳግም ሞት የለበትም፡፡ በፍጻሜ ዘመኑ ከዚህ ዓለም ተለይቶ ወደ ወዲያኛው ዓለም በሚሸጋገርበት ጊዜም ወደ ገነት እንጅ ወደ ሲኦል አይወርድም፡፡ ወደ ሲኦል ቢሄድም እንኳ ልትቀበለው አትችልም፤ ምክንያቱም በሕይወተ ሥጋ ሳለ በደመ ክርስቶስ ታትሟልና፡፡

‹‹እመን እንጂ አትፍራ›› (ማር. ፭፥፴፮)

በክርስቶስ ክርስቲያን ለተባልን ለእኛ ለኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ሃይማኖት ተከታዮች እምነት የድኅነታችን መሠረት ነው፤ በፈተናና መከራ ለተሞላው ክርስቲያናዊ ሕይወታችን ለጠላት ከመሸነፍም ሆነ በኃጢአት ከመውደቅ የሚያድነን እንዲሁም በተስፋ ነገን እንድንጠብቅ የሚረዳን እምነታችን ነው፡፡ ዘወትር በጸሎት አምላካችን ድኅነተ ሥጋን እና ድኅነተ ነፍስን ለምንማጸን እርሱ እግዚአብሔር ቸርነቱና ምሕረቱ የበዛ ነው፡፡

‹‹አንተ አምላኬና መድኃኒቴ ነህና›› (መዝ. ፳፬፥፭)

ነቢዩ ዳዊት በመዝሙሩ እንደተማጸነው
ድኅነትን ዐውቆ እንደተነበየው
አንተ ነህ መድኃኒት እስከመጨረሻው

‹‹ትፈወሱም ዘንድ እያንዳንዱ ሰው ስለ ሌላው ይጸልይ፤ የጻድቅ ሰው ጸሎት በሥራዋ እጅግ ኃይል ታደርጋለች›› (ያዕ. ፭፥፲፮)

እዚህ ላይ ማስተዋል ያለብን አምላካችንን በሕይወት ዘመናቸው ሁሉ ሌት ከቀን ያለማቋረጥ በጸሎት፤ በጾም እና በስግደት ያገለገሉ ቅዱሳን አባቶቻችንን በማሰብ ለኃጢአተኞች ምሕረትን እንደሚያደርግ ነው፡፡ በተለይም ጻድቁ አባታችን አቡነ እስትንፋሰ ክርስቶስ ተጋድሏቸውን ሲፈጽሙ በተሰጣቸው ቃል ኪዳን መሠረት እኛን ከቸነፈር እንደሚጠብቁን በማሰብ ልንጽናና ይገባል፡፡ …..
እንዲሁም ሕፃኑ ቂርቆስ በሰማዕትነት ባረፈበት ዕለት ‹‹…ስምህ በተጠራበት፣ ቤተ መቅደስህ በታነጸበት ሥዕልህ ባለበት ቦታ ሁሉ የሕፃናት እልቂት፣ የከብት በሽታ፣ የእህል እጦት፣ ረኃብ፣ ቸነፈር አይደርስም›› የሚል ቃል ኪዳን ሰጥቶታል፡፡

‹‹እግዚአብሔር ይቅርታን ይረሳልን? በቁጣውስ ምሕረቱን ዘጋውን?›› (መዝ. ፸፮፥፱)

ብዙዎች በአሁኑ ሰዓት ስጋትና ጭንቀት ላይ ናቸው፤ ነቢየ እግዚአብሔር ዳዊት ‹‹እግዚአብሔር ይቅርታን ይረሳልን? በቁጣውስ ምሕረቱን ዘጋውን?›› ብሎ በጸሎት እንደጠየቀው አዛውንቶችም የዚህ መቅሰፍት ማብቂያ የሚቆምበትን ጊዜ በመመኘት አምላካቸው ስለምን ቸል እንዳለ ሲጠይቁ ይሰማሉ፤ ምሕረትንም እንዲያበዛልን አብዝተው ሲለምኑ ይደመጣሉ፡፡ (መዝ. ፸፮፥፱)

ደብረ ምጥማቅ

ነቢየ እግዚአብሔር ዳዊት “ወለገጽኪ ይትመሐለሉ ኲሎሙ አሕዛብ ብዑላነ ምድር፤ የምድር ባለጠጎች አሕዛብ ሁሉ በፊትሽ ይማለላሉ፤” በማለት ትንቢትን እንደተናገረላት ብዙዎች ቅዱሳን ቅድስት ድንግል ማርያምን ተገልጻላቸው ለማየት ተመኝተዋል፤ ልመናቸው ተሰምቶላቸው የአምላክ እናት ተገልጻላቸው እጅግ አስደናቂ ውበቷን አይተዋል፡፡ ከነዚህ ውስጥ በደብረ ምጥማቅ የነበሩ ምእመናን ሌሎችም ብዙዎች ንጹሓን ክርስቲያኖች ይገኙበታል፡፡ (መዝ. ፵፬፥፲፪;)