«የተራቡትን ከበረከቱ አጠገባቸው» /ሉቃ. ፩፥፶፫/

በፍጡራን አንደበት ተነግሮ ስለማያልቅ ክብሯና ልዕልናዋ ክብር ምስጋና ይድረሳትና ይህንን ኀይለ ቃል የተናገረችው አምላክን የወለደች በድንጋሌ ሥጋ በድንጋሌ ነፍስ የጸናች ክብርት እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ናት። ወንጌላዊው ሉቃስ በወንጌሉ ጸሎተ እግዝእትነ ማርያምን እንደ ጻፈልን እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ብዙ ኀይለ ቃላት ያላቸውን ምሥጢራት በዚህ ክፍል ተናግራለች። ይህ የተናገረችው  ኀይለ ቃል በውስጡ ብዙ መንፈሳዊ፣ ሰማያዊ ትርጉም አለው። ምልእተ ጸጋ፣ምልእተ ውዳሴ፣ምልእተ ክብር የሆነች እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም በዚህ የጸሎት ክፍል ከተናገረችው ብዙ ወርቃማ ቃላት  መካከል ለትምህርታችን «የተራቡትን ከበረከቱ አጠገባቸው» የሚለውን ኃይለ ቃል እንመለከታለን። ይህንን ኀይለ ቃል እመቤታችን ስለ ሦስት ነገር ተናግራዋለች፤ እነርሱም የሚከተሉት ናቸው።

‹‹መጠራጠር የእምነትና የጽናት ጉድለት ነው›› ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ሺኖዳ ሣልሳዊ

መጠራጠር የእምነትና የጽናት ጉድለት ነው፤ መድኃኒታችን ኢየሱስ በባሕር ላይ እየሄደ ወደ ደቀ መዛሙርቱም በመጣ ጊዜ ምትሐት ምስሎአቸው ታወከው በፍርሃት ጮኹ።  ጌታችን ኢየሱስም ‹‹አይዞአችሁ፥ እኔ ነኝ አትፍሩ›› አላቸው፤  ቅድስ ጴጥሮስም መልሶ፥ አቤቱ፥ አንተስ ከሆንህ በውኃው ላይ ወደ አንተ እንድመጣ እዘዘኝ›› አለው። እርሱም ‹‹ና›› አለው። ጴጥሮስም ከታንኳው ወርዶ ወደ ኢየሱስ ሊደርስ በውኃው ላይ ሄደ።  ነገር ግን ነፋሱ በርትቶ ባየ ጊዜ ፈራ፥ ሊሰጥምም በጀመረ ጊዜ ጌታ ሆይ፥ አድነኝ ብሎ ጮኸ። ወዲያውም ጌታችን ኢየሱስ እጁን ዘርግቶ ያዘው ‹‹አንተ እምነት የጎደለህ፥ ስለምን ተጠራጠርህ?›› ብሎታል፡፡ መጠራጠር ያለመጽናት፣ ያለማመን ውጤት ነውና፡፡ (ማቴ. ፲፬፥፳፬-፴፩)

‹‹በሞት ጥላ መካከል እንኳ ብሄድ፤ አንተ ከእኔ ጋር ነህና ክፉን አልፈራም፤ በትርህና ምርኩዝህ እነርሱ ያጽናኑኛል›› (መዝ. ፳፪፥፬)

ዓለም በኃጢአት እና ክፋት ተሞልታ በሰይጣን አገዛዝ ሥር ከሆነች ውላ አድራለች፤ የሰይጣን ሥራ ከዳር እስከዳር ተስፋፍቶ በበዛበት ወቅት ሰዎች የርኩስ መንፈስ ቁራኛ በመሆን የመከራ አረንቋ እየተፈራረቀባቸው ይገኛሉ፡፡ ጦርነት፣ ቸነፈር፣ ረኃብ፣ በሽታና ሥቃይ እንግልትም እየደረሰባቸው ነው፡፡

“ሃይማኖትና ሀገር ወጣት ሲረከበው ነው ሀገርነቱም፣ እምነቱም ሊቀጥል የሚችለው”

የዛሬው የቤተ አብርሃም እንግዳችን መጋቤ ምሥጢር ቀሲስ ቀጸላ ፈንቴ ይባላሉ፡፡ ከአባታቸው ከቄስ ፈንቴ ታረቀ እና ከእናታቸው ከወይዘሮ ጎንደር በቀለ በ፲፱፻፶፰ ዓ.ም በምዕራብ ጎጃም ሰከላ ወረዳ ልዩ ስሙ ጉሌ ኪዳነ ምሕረት ተብሎ  በሚጠራ ቦታ ተወለዱ፡፡ በአብነት ትምህርቱ ቅኔን ጨምሮ ሌሎቹንም ትምህርቶች ተጨልፎ ከማያልቀው ከቤተ ክርስቲያን ማዕድ በአባቶች እግር ሥር ቁጭ ብለው ተምረዋል፡፡ ወደ አዲስ አበባ በመምጣትም በሰዋሰው ብርሃን ቅዱስ ጳውሎስ የካህናት ማሠልጠኛ ለአራት ዓመት የነገረ መለኮት ትምህርት ተምረዋል፡፡ በትውልድ አካባቢያቸው ለ፲፫ ዓመት የቅኔና የሐዲሳት መምህር ሆነው አገልግለዋል፣ ከዚያም ወደ ከተማ በመምጣት ከ፳፪ ዓመታት በላይ የቅኔ፣ የሐዲሳትና የብሉያት መምህር ሆነው ያገለገሉ ሲሆን፣ በርካታ ተማሪዎችን አስተምረው ለአገልግሎት አብቅተዋል፡፡ በአጠቃላይ ባሳለፉት የአገልግሎት ዘመን የቅኔና የትርጓሜ መምህር ሆነው በማገልገል ከ፴፱ ዓመት በላይ አስቆጥረዋል፡፡ በአሁኑ ወቅት የሃይማኖተ አበው ትምህርታቸውን በመከታተል ላይ ይገኛሉ፡፡ ከመጋቤ ምሥጢር ቀሲስ ቀጸላ ፈንታ ጋር በሕይወት ተሞክሯቸው ዙሪያ ልምዳቸውን፣ እንዲሁም ተያያዥ ጉዳዮች ያጋሩን ዘንድ የቤተ አብርሃም እንግዳችን አድርገናቸዋል፤ መልካም ንባብ፡፡

ማማተብ

ሰላም ልጆች እንደምን አላችሁ? ደኅና ናችሁ? መቼም እግዚአብሔር ይመስገን እንዳላችሁ  ተሰፋ አደርጋለሁ፡፡ ልጆች ምንጊዜም ቢሆን እግዚአብሔርን ማመስገን መዘንጋት የለብንም እሺ?  ምክንያቱም እኛ ሰዎች የተፈጠርነው  ለምስጋና ስለሆነ ነው፡፡ ስለሆነም ልጆች በዚህ ክፍል በአጭሩ ሰለ ማማተብ እንማማራለን፡፡ እስኪ ስለማማተብ ምን ታውቃላችሁ ልጆች? የማማተብ ትርጉሙስ ምንድ ነው ትላላችሁ? እንግዲያውስ ዛሬ ስለማማተብ አጭር መርጃ ይዠላችው ቀርቤለሁ፤ መልካም ንባብ ይሁንላችሁ፡፡

እንኳን ለሊቀ መላእክት ቅዱስ ሚካኤል ክብር በዓል አደረሰን!

የዚህን ታላቅ የከበረ የመላእክት አለቃ ሚካኤልን የበዓሉን መታሰቢያ ለማድረግ መታገል ይገባናል፤ እርሱ ከሰይጣን ወጥመድ ያድነን ዘንድ፤ በዘመናችን ሁሉም ይጠብቀን ዘንድ፤ ኃጢአታችንንም ያስተሠርይ ዘንድ፤ መከራችንንም ያርቅ ዘንድ፤ የምድራችንንም ፍሬ ይባርክ ዘንድ፤ ፈቃዱንም ለመሥራት ይረዳን ዘንድ፤ ከእኛ ወገን የሞቱትን ዕረፍተ ነፍስ ይሰጥ ዘንድ፤ ወደ መንገድ የሔዱ አባቶቻችንና ወንድሞቻተንን ወደ ቤቶቻቸው በሰላም በጤና ይመልሳቸው ዘንድ፤ በመካከላችንም ፍቅር ያደርግልን ዘንድ፤ እስከ መጨረሻዪቱም ሕቅታ ድረስ በቀናች ሃይማኖት ያጸናን ዘንድ፤ በእግዚአብሔር ፊት ስለ እኛ ይለምናልና፡፡

‹‹በሕማም፣ በመከራና መሥዋዕት በመሆን ፍቅራችን ይፈተናል›› ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ሺኖዳ ሣልሳዊ

ፍቅርን የሚያውቅ ሰው ለእግዚአብሔር እና ለሌሎች ራሱን መሥዋዕት አድርጎ ያቀርባል፡፡ ሰው በመጀመሪያ መሥዋዕት ለማድረግ መልመድ ያለበት ከእርሱ ውጪ በሆኑ ነገሮች ማለትም ገንዘቡን፣ ጊዜውን እና ሀብቱን በመለገስ ነው፤ መስጠት ከመቀበል አንድ ነውና፡፡ ለሰዎች ደስታ እንደራሱ የሚጨነቅ እርሱ ፍቅርን ያውቃል፤ እግዚአብሔርም ከእርሱ ጋር ይኖራል፡፡ መሥዋዕትነት መክፈል ካልቻልን ግን ፍቅር አልገባንም ማለት ነው፤ አምላካችን እግዚአብሔርን ማፍቀር ካልቻልን ደግሞ ድኅነተ ሥጋንም ሆነ ድኅነተ ነፍስን ማግኘት አንችልም፡፡

‹‹ሰላምን እተውላችኋለሁ፤ ሰላሜን እሰጣችኋለሁ›› (ዮሐ. ፲፬፥፳፯)

ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በወንጌል ለሕዝቡ ‹‹ሰላምን እተውላችኋለሁ፤ ሰላሜን እሰጣችኋለሁ…›› ብሎ በነገራቸው ቃሉ ሰላምን የሚሰጠው እርሱ እንደሆነ እንረዳለን፤  ይህም የተወልን ሰላም መንፍሰ ቅዱስ በመሆኑ መንፈስ ቅዱስ በአንድ ሰው ውስጥ ሲያድር የልብ ሰላምን ይጎናጸፋል፡፡ ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ ስለዚህ ሰላም ሲጽፍ እንዲህ ብሏል፤‹‹አእምሮውንም ሁሉ የሚያልፍ የእግዚአብሔር ሰላም ልባችሁንና ሀሳባችሁን በክርስቶስ ኢየሱስ ይጠብቃል፤›› (ዮሐ. ፲፬፥፳፯፤ ፊል. ፬፥፯)

ግስ

ውድ አንባብያን በአለፈው ክፍለ ጊዜ የቤት ሥራ መስጠታችን ይታወቃል፡፡ እናንተም መልሱን በትክክል ሠርታችሁ እንደምትጠብቁን ተስፋ እናደርጋለን፡፡ ለማረጋገጥ ያህል ጥያቄዎቹን እናስታውሳችሁና መልሱን እንደሚከተለው አስቀምጠነዋል፡፡ የሚከተሉትን ግሶች በቀዳማይ አንቀጻቸው በዐሥሩም መራሕያን አርቧቸው። 

‹‹የሚሰማኝ ግን በተስፋ ይኖራል፤ ከክፉም ሁሉ ያለድንጋጤ ያርፋል›› (ምሳ.፩፥፴፫)

የእስራኤል ንጉሥ ጠቢቡ ሰሎሞን በግዛቱ ዘመን ለሕዝቡ በምሳሌ ቃሌን ስሙ እያለ በተደጋጋሚ ይናገር ነበር። ነገር ግን የእርሱን ሳይሆን የእግዚአብሔርን ቃል ነው፡፡ የእግዚአብሔርን ቃልን መስማት ደግሞ ጥበበኛ ያደርጋል፤ ተስፋን ያለመልማል፤ ከክፉም ይታደጋል። ስለዚህ ‹‹ቃሌን የሚሰማ ግን በተስፋ ይኖራል፤ ከክፉም ሁሉ ያለድንጋጤ ያርፋል›› በማለት ያስረዳናል። በዚህ ኃይለ ቃል የእግዚአብሔርን ቃል መስማት፣ በተስፋ መኖርና ከክፉ መዳን የሚሉ መሠረታዊ ነጥቦችን እናገኛለን፤ እያንዳንዳቸውን እንመልከታቸው። (ምሳ.፩፥፴፫)