‹‹ጊዜ ዕረፍታ ለሶልያና››

እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም በምድር ላይ በአይሁድ ክፋት ብዙ መከራና ኃዘንን ካሳለፈች በኋላ በዘመነ ሉቃስ ጥር ሃያ አንድ ቀን በስድሳ አራት ዓመቷ ወደ ዘለዓለም ደስታ ትገባ ዘንድ ዐርፋለች፡፡

ጸሎትና ክርስቲያናዊ ሕይወት

ጸሎት ክርስቲያኖች ከሚያከናውኗቸው መንፈሳዊ ተግባራት ውስጥ አንዱ ነው፡፡ ክርስቲያን በጸሎት የሚተጋ ሰው ነው፤ ያለ ምግብ ሰው መኖር እንደማይችል ሁሉ ክርስቲያንም ያለ ጸሎት መኖር አይችልም፡፡ ከውኃ ውስጥ የወጣ ዓሣ ሕይወት እንደማይኖረው ሁሉ ከጾም ከጸሎት እና ከንስሓ ሕይወትም የተለየ ክርስቲያን የሞተ ነው፤ ሕይወት የሌለው በነፋስ ብቻ የሚንቀሳቀስ በድንም ይሆናል፤ መጸለይ ሕይወት ነውና፤ አለመጸለይ ደግሞ የነፍስ ሞት ነው፡፡

ሰማዕታት ቅድስት ኢየሉጣ እና ሕፃን ቂርቆስ

ቅድስት ኢየሉጣ በሮም ግዛት በሚገኝ አንጌቤን በሚባል አገር በፈሪሃ እግዚአብሔር፣ በክርስትና ሃይማኖት እና በበጎ ምግባር ጸንታ ትኖር የነበረች ደግ ሴት ነበርች፡፡ በሥርዓት ያሳደገችው ቂርቆስ የሚባል ሕፃን ልጅም ነበራት፡፡

‹‹ከዚህም በረት ያልሆኑ ሌሎች በጎች አሉኝ፤ እነርሱን ደግሞ ላመጣ ይገባኛል፤ ድምጼንም ይሰማሉ፥ አንድ መንጋም ይሆናሉ እረኛውም አንድ ነው›› (ዮሐ. ፲፥ ፲፮)

ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በአንቀጸ አባግዕ ሲያስተምር ‹‹ከዚህም በረት ያልሆኑ ሌሎች በጎች አሉኝ፤ እነርሱን ደግሞ ላመጣ ይገባኛል፤ ድምጼንም ይሰማሉ፥ አንድ መንጋም ይሆናሉ እረኛውም አንድ ነው›› ብሏል።(ዮሐ. ፲፥ ፲፮)

ጥምቀተ ክርስቶስ

በቅዱስ ዮሐንስ እጅ በማየ ዮርዳኖስ ተጠምቆ የባሕርይ ልጅነቱንና አምላክነቱን ከአብ እና ከመንፈሰ ቅዱስ አስመሰከረ፡፡

ዘመነ አስተርእዮ

አስተርእዮ መታየት ወይም መገለጥ የሚል ትርጓሜ ያለው የግእዝ ቃል ነው፡፡ በግሪክ ‹‹ኤጲፋኒ›› የሚል ስያሜ አለው፤ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ሊቃውንትም ይህን ቃል በመጠቀም ኤጲፋኒያ እያሉ በዜማ መጻሕፍቶቻቸው ይጠሩታል፡፡

በዓለ ግዝረት

በዚህ ጊዜ ጌታችን ዐይኖቹን ወደ ሰማይ አቅንቶ ‹‹አባት ሆይ ለአብርሃም፣ ለይስሐቅ፣ ለያዕቆብ አስቀድሞ ግዝረትን የሰጠሃቸው፤ ያቺን ግዝረት ዛሬ ለእኔ ስጠኝ›› አለ፡፡ ያንጊዜም ያለ ሰው እጅ በጌታችን ላይ ግዝረት ተገለጠ (የግዝረት ምልክት ታየ)፡፡

‹‹ለራስህ እና ለትምህርትህ ተጠንቀቅ›› (፩ኛ ጢሞ. ፬ ፥፲፮)

በአሁኑ ወቅት በአንድም በሌላ አንዳንድ የይዘት፣ የትርጉም፣ የፍቺ ግድፈቶች ከዛ የባሰም የዶግማ ችግር ያለባቸው ለቤተክርስቲያን ትምህርት ስጋት የሆኑ ከስንዴ መሐል የተቀላቀሉ ጥቂት እንክርዳድ የተቀላቀለባቸው መጻሕፍት በቤተ ክርስቲያን ስም እየወጡ ነው፡፡ ስለዚህ እንክርዳዱን ከስንዴው ለቅሞ መለየትና ማረም ያስፈልጋል፡፡

‹‹የገሃነም ደጆችም አይችሏትም›› (ማቴ.፲፮፥፲፰)

ጌታችን ኢየሱስም መልሶ እንዲህ አለው ‹‹የዮና ልጅ ስምዖን ሆይ÷ በሰማያት ያለው አባቴ እንጂ ሥጋና ደም ይህን አልገለጠልህምና ብፁዕ ነህ፡፡ እኔም እልሃለሁ÷ አንተ ጴጥሮስ ነህ፤ በዚያች ዓለት ላይ ቤተ ክርስቲያኔን እሠራለሁ÷ የገሃነም ደጆችም አይችሏትም፡፡››(ማቴ.፲፮፥፲፫—፳)