tenat 2006 1

የማኅበረ ቅዱሳን ጥናትና ምርምር “የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን ሚና በፀረ ቅኝ ግዛት ትግል” በሚል ርእስ ጥናት አቀረበ

 የካቲት 24 ቀን 2006 ዓ.ም.

መ/ር ሳሙኤል ተስፋዬ

tenat 2006  1
“የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ሚና በፀረ ቅኝ ግዛት ትግል” በሚል ርዕስ በማኅበረ ቅዱሳን ጥናትና ምርምር ዋና ክፍል አዘጋጅነት በአቶ አለማ ሐጎስ አቅራቢነትና በአቶ አበባው አያሌው አወያይነት በማኅበሩ የመሰብሰቢያ አዳራሽ የካቲት 22 ቀን 2006 ዓ.ም ቀረበ፡፡

tenat 2006  2ጥናቱ ያተኮረው የኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን በፀረ ቅኝ ግዛት ትግል ወቅት ያደረገችውን አስተዋጽኦ የዳሰሰ ሲሆን በዋናነት፡-

  • ለአፍሪካና ለጥቁር ሕዝቦች የነጻነት ትግል በር የከፈተች መሆኗና የኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን በአፍሪካውያን መፈለጓና ቤተ ክርስቲያን መመስረታቸውን፡፡
  • በጦርነት ዘመቻ የሃይማኖቱ መሪዎችና ተከታዮቹ እግዚአብሔርን መከታ አድርገው መዝመታቸው፡፡
  • የኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን ሀገር ለመውረር የመጣን ጠላት በመመከት ግንባር ቀደም ሆና ለአንድነትና ለነጻነት መታገሏ፡፡
  • የኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን ከድል በኋላ በምርኮኞች አያያዝ ላይ ያደረገችው አስተዋጽኦና ሌሎችም ዐብይ ጉዳዮች በጥናት አቅራቢው ከቀረቡ በኋላ ከተሳታፊዎች ጥያቄና አስተያየትtenat 2006  3 ቀርበዋል፡፡በውይይቱ የኢትዮጵያ አባት አርበኞች፣ ምሁራንና የማኅበረ ቅድሳን አባላት ተገኝተዋል፡፡