Baptism

“ግብረ ፊልጶስ” የተሠኘ ሲምፖዚየም እንደሚዘጋጅ ተገለጸ

ታኅሣሥ 05 ቀን 2006 ዓ.ም.

በእንዳለ ደምስስ

 

“ግብረ ፊልጶስ – ሐዋርያዊ ጉዞ በኢትዮጵያ በቀድሞው፤ በመካከለኛውና በአሁኑ ዘመን” በሚል መንፈሳዊ ጉባኤ በማኅበረ ቅዱሳን ትምህርትና ሐዋርያዊ አገልግሎት ዋና ክፍል የስብከተ ወንጌል ማስፋፊያ አማካይነት ሲምፖዚየም እንደሚዘጋጅ ተገለጸ፡፡ Baptism

 

ተኅሣሥ 12 እና 13 ቀን 2006 ዓ.ም. ከቀኑ 8፡00 ሰዓት ጀምሮ በቅድስት ሥላሴ መንፈሳዊ ኮሌጅ ስብከተ ወንጌል አዳራሽ በሚካሔደው ሲምፖዚየም ላይ ከዚህ በፊት በተልተሌ፤ ጂንካ፤ ከረዩ፤ መተከልና ግልገል በለስ አካባቢዎች ተጠምቀው የእግዚአብሔር ልጅነትን ያገኙ ምእመናን በአካል በመገኘት በጉባኤው ላይ አሁን ያሉበትን ሁኔታ ያቀርባሉ፡፡

Baptism1የስብከተ ወንጌል ማስፋፊያ ክፍሉ ያከናወነውን የአራት ዓመታት የሥራ ሪፖርት፤ እንዲሁም ጥናታዊ ጽሑፍ የሚቀርቡ ሲሆን በጥናታዊ ጽሑፉ ላይና ወደፊት ሊሠሩ በታቀዱ ሥራዎች ላይ ውይይት ይካሔድባቸዋል፡፡ በተጨማሪም ከዚህ ቀደም ተጠምቀው ነገር ግን በአጥቢያቸው ቤተ ክርስቲያንና ሰንበት ትምህርት ቤት ለሌላቸው የገቢ ማሰባሰቢያ መርሐ ግብር ይከናወናል፡፡

ይህንን መርሐ ግብር በማኅበሩ ድረ ገጽ (www.eotcmk.org) ላይ የቀጥታ ዓለም አቀፍ ሥርጭት የሚተላለፍ በመሆኑ ምእመናን መከታተል እንደሚችሉ ክፍሉ አስታውቋል፡፡