የአሰቦት ገዳምን ለመርዳት ጉባኤ ሊካሄድ ነው፡፡

ግንቦት 8/2004 ዓ.ም.

በእንዳለ ደምስስ

የአሰቦት ደብረ ወገግ ቅድስት ሥላሴና አቡነ ሳሙኤል ገዳምን ለመርዳት ታላቅ መንፈሳዊ ጉባኤ በጠቅላይ ቤተ ክህነት ስብከተ ወንጌል አዳራሸ ሰኔ 3 ቀን 2004 ዓ.ም. ከቀኑ 7 ሰዓት ጀምሮ ይካሄዳል፡፡ ከ800 ዓመታት በላይ እድሜ ያስቆጠረው ገዳም በፃድቁ አቡነ ሳሙኤል ዘደብረ ወገግ የተመሠረተ ሲሆን በቅርቡ የገዳሙ ደን  ተቃጥሎ ከፍተኛ ጉዳት የደረሰበት መሆኑ ይታወሳል፡፡

ገዳሙ ከከተማው 18 ኪ. ሜትር ርቀት ላይ የሚገኝ ሲሆን ቅድስት ሥላሴ ቤተ ክርስቲያን ለመድረስ 6 ኪሎ ሜትር ርቀት ያለውን ተራራ በእግር መውጣት ይጠበቃል፡፡ የመንገዱ አስቸጋሪነት ገዳሙን የልማት ተጠቃሚ ለማድረግ ያላስቻለው ሲሆን መንገዱን ለመሥራት ኮሚቴ በማዋቀር እንቅስቃሴ ተጀምሯል፡፡ ምዕመናን ይህንን ጥንታዊና ታሪካዊ ገዳምን ለመርዳት ትኬቱን በመግዛት ክርስቲያናዊ ግዴታቸውን እንዲወጡ የገዳሙ አስተዳደር ጥሪውን ያቀርባል፡፡