አሥረኛው ጠቅላላ ጉባኤ ተራዘመ

ነሐሴ 24 ቀን 2004 ዓ.ም.

በእንዳለ ደጀኔ

ከነሐሴ 26-28 ቀን 2004 ዓ.ም. ሊካሄድ የነበረው የማኅበረ ቅዱሳን አሥረኛ ጠቅላላ ጉባኤ ወደ ነሐሴ 30 ቀን 2004 ዓ.ም. ተራዘመ፡፡

 

በኢፌዲሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ክቡር አቶ መለስ ዜናዊ ኅልፈተ ሕይወት ምክንያት ብሔራዊ የሃዘን ቀን በመሆኑ ጉባኤው እንዲራዘም መደረጉን የጠቅላላ ጉባኤው አዘጋጅ አብይ ኮሚቴ ሰብሳቢ አቶ የሺዋስ ማሞ ገልጸዋል፡፡

 

ዘንድሮ የሚካሄደው ጠቅላላ ጉባኤ 1 ሺህ ተሳታፊዎች የሚታደሙበት ሲሆን ለቀጣዩ 4 ዓመታት ማኅበሩን የሚመራ አዲስ አመራር እንደሚመረጥም አቶ የሺዋስ ማሞ ጨምረው ገልጸዋል፡፡

 

ጠቅላላ ጉባኤው እስከ ጳጉሜ 2 ቀን 2004 ዓ.ም. ይቀጥላል፡፡