በኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ/በሰ/ት/ቤቶች ማ/መምሪያ -  ማኅበረ ቅዱሳን
  • ቀዳሚ ገጽ
  • ስለ ማኅበሩ
    • ማእከላት
      • ሰሜን አሜሪካ
      • አውሮፓ
      • ሩቅ ምሥራቅ
      • ደቡባዊ አፍሪካ
      • የካናዳ ማእከል
      • አዲስ አበባ ማእከል
        • የወርሃዊ አስተዋጽኦ መሰብሰቢያ
    • ኅትመት እና ሚዲያ
      • ሐመር እና ስምዐ ጽድቅ
      • ማኅበረ ቅዱሳን ቲቪ
      • የማኅበረ ቅዱሳን ዩቲዉብ
      • መጽሔተ ተልዕኮ
      • ማእከለ ሥዕላት
        • ካሜራው ምን ይላል
        • የቅዱሳት ሥዕላት ማኅደር
  • ትምህርቶች
    • የርቀት ትምህርት
    • ስብከት
    • መሠረታዊ የቤተ ክርስቲያን ትምህርቶች
  • ግቢ ጉባኤ
  • ሌሎች ድረ ገጾች
    • በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን መንበረ ፓትርያርክ የብፁዕ ወቅዱስ ልዩ ጽ/ቤት ድረ ገጽ
    • በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ድረ ገጽ
    • በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ሰንበት ት/ቤቶች ማደራጃ መምሪያ ድረ ገጽ
  • ቋንቋ
    • አማርኛ
    • ትግርኛ
    • ወላይትኛ
    • ሲዳምኛ
    • Affan Oromo
    • English
  • ያግኙን
  • Click to open the search input field Click to open the search input field Search
  • Menu Menu

ማኅበራዊ ሕይወት

You are here: Home1 / ክርስቲያናዊ ሕይወትና ሥነ ምግባር2 / ማኅበራዊ ሕይወት

‹‹ቢቻላችሁስ ከሰው ሁሉ ጋር በሰላም ኑሩ›› (ሮሜ. ፲፪፥፲፰)

በለሜሳ ጉተታ

ማኅበራዊ ሕይወት የአንድነት፣ የመቻቻል እና የመደጋገፍ ኑሮ ነው፤ የቤተ ክርስቲያን አስተምሮ በማኅበራዊ ሕይወት ውስጥ መተሳሰብ፣ መረዳዳትና መተጋገዝ እንዳለብን ያስረዳል፡፡ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ እንዳሉት ‹‹ማኅበራዊ ሕይወታችን የሰላም፣ የፍቅር፣ የአንድነት፣ የመተሳሰብ፣ የመከባበር፣ የመተጋገዝ፣ ምንጭ ስለሆነ የእርስ በርስ ግጭትን በማራቅ ሰላማዊ፣ የለመለመ አካባቢ፣ የለማ ሀገር እንዲኖረን ትልቅ እና መሠረታዊ አስተዋጽኦ አለው››፡፡ ይህም ኃላፊነትና አደራን መወጣት ነው፡፡ ቅዱሳን አባቶቻችን ሀገርን፣ ቤተ ክርስቲያንን፣ ታሪክን፣ ትውፊትን፣ ሥርዓትን ለእኛ ያስረከቡን የክርስትና ፍቅር፣ ውለታና አደራ ስላለባቸው ባለ ራእይና ሩቅ አሳቢ በመሆናቸውም ጭምር ነው፡፡ ክርስቲያኖች ይህን አደራ ተቀብለው የቤተ ክርስቲያን ሥርዓትን በመጠበቅ በኅብረት ለመኖር ክርስቲያናዊ ምግባሮችን የመፈጸም ኃላፊነት አለባቸው፡፡

ዘረኝነት፣ ለዝሙት መገዛት፣ ዕርቅ፣ ሰላምና ፍቅርን አለመፈለግ፣ ትዳርና ቤተሰብን መበተን፣ ክርስቲያናዊ ግዴታን አለመፈጸም እና ከክርስትና ሕይወት መራቅ የመንፈሰዊ ሰው ምግባር አይደለም፡፡ መጽሐፍ ቅዱስ በሮሜ. ፲፪፥፲፰ ላይ ‹‹ቢቻላችሁስ ከሰው ሁሉ ጋር በሰላም ኑሩ›› በማለት መክሯል፤ ክርስትና ፍቅር ነውና፡፡ ያለምንም አድልዎ ሰውን ሁሉ ሳንንቅ በማክበር፣ በሰው ላይም ችግርን ሳንፈጥርና ተንኮልን ሳንሠራ መኖር አለብን፤ ይህ ደግሞ ክርስቲያናዊ መሠረት ነው፡፡

ማኅበራዊ ጉዞ በእምነትና በእውነት ላይ የተመሠረተ ሲሆን ለበረከት ይሆናል፡፡ ሥራችንን በትጋት፣ በቅንነት፣ በታማኝነት እንዲሁም በታዛዥነት ልንፈጽም ይገባል፡፡ ትዳራችን በእግዚአብሔር ፈቃድ ሲጸና፣ መልካም ቤተሰብ ስንመሠርት፣ የታመሙትንና የተቸገሩትን ስንጠይቅና ስናስተዛዘን፣ የተራቡትን ስናበላና ስናጠጣ፣ ተዝካር ስናወጣ፣ ችግሮቻችንን ለመቅረፍ በአንድነት ውይይት ስናደርግ፣ ቅዱሳንን፣ ጻድቃንና ሰማዕታትን ስንዘክር እንዲሁም የቡሄ (ደብረ ታቦር) እና የደመራ (የመስቀል) በዓላትን በአንድነት ስናከብር፤ ማኀበራዊ ሕይወታችን ጠንካራ ይሆናል፡፡ ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስም የማኀበራዊ ሕይወት ጠቀሜታን ሲገልጽ ‹‹ደስ ከሚለው ጋር ደስ ይበላችሁ፤ ከሚያለቅሰው ጋርም አልቅሱ፡፡›› ብሏል (ሮሜ. ፲፪፥፲፭)

በሐዲስ ኪዳን በሐዋርያት ስብከት ያመኑ ምእመናን በአንድ ልቡናና በአንድ ሐሳብ ተስማምተው ይኖሩ ነበር፡፡ ያላቸውንም ሀብት የሚያስቀምጡት በጋራ እንጂ በግል አልነበረም፡፡ ንብረታቸውን በሙሉ እየሸጡ ገንዘባቸውን ሰብስበው በሐዋርያት እግር ስር ያስቀምጡ ነበር፡፡ ‹‹ያመኑትም ሁሉ አንድ ልብና አንዲት ነፍስ ሆነው ይኖሩ ነበር፤ በውስጣቸውም የሁሉ ገንዘብ በአንድነት ነበር እንጂ ‹ይህ የእኔ ገንዘብ ነው› የሚል አልነበረም››፡፡ (ሐዋ.፬፥፴፪)

ማኅበራዊ ሕይወት የጽድቅ፣ የቅድስና፣ የበረከት ሥራን የምንሠራበት እና ለዘለዓለም ሕይወትና ክብር የሚያበቃንን ሥራ የምንፈጽምበት ነው፡፡ ለስንፍናችን ሰበብ ማቅረብ የእግዚአብሔርን ጸጋና በረከትን ያሳጣል፤ ሰላም የሰፈነበት ሕይወት እንድንኖር አያደርግም፡፡ ሁሉ ጊዜ ሕይወትን በሀሳብ፣ በጭንቀት፤ በጉድለት ለመምራት ይዳርጋልና ወደ ልቦናችን መመለስ አለብን፡፡ ፩ኛ ጢሞቴዎስ ፮፥፳ ላይም ‹‹የተሰጠህን አደራ ጠብቅ›› ማለቱ ማንነትን ያለመርሳት ኃላፊነት እና አደራን መወጣት እንዲሁም ለሌሎች ሰዎች መድረስ እንዳለብን ስለሚያሳይ ልንማርበትና በሕይወትም ልንኖርበት ይገባል፡፡

ተምረው ማገልገል ያቃተቸው፣ የጠፉ፣ በዓለም ጉያ ሥር የተሸሸጉ፣ ከቤተ ክርስቲያን እና ከንስሓ ሕይወት የሸሹ ሰዎች የክርስትና ክብር ስላልገባቸው ነው፡፡ የክርስትና ክብር የገባው ለሥጋ ምቾት ቦታ አይሰጥም፡፡ ነፍሱን ያስበልጣል፤ ከሁሉም ነገር ይልቅ ለክርስትና ሕይወቱ ቅድሚያ ይሰጣል፤ ራሱን አሳልፎም ለአምላኩ ይሰጣል፡፡ ሆኖም ዛሬ ብዙዎች በዓለም ጠፍዋል፤ ማንነታቸውን ረስተዋል፤ በዚህም ለዲያብሎስ ለሥጋ ፈቃድና አምሮት ተገዝተዋል፡፡ እንኳን በእኛ በአሕዛብ ዘንድ የማይሠሩ በዓይን ለማየትና በጆሮ ለመስማት አሰቃቂ የሆነ ሰይጣናዊ ሥራዎችን በመሥራት ላይ ይገኛሉ፤ ስለዚህም ወደ ልቡናችን መመለስ ይኖርብናል፡፡

ዛሬ ሰዎች በኅብረትም ሆነ በግል የረከሰ ሥራ እየሰሩ ይገኛሉ፤ ጫት የሚቅሙ፣ ሲጋራ የሚያጤሱ፣ አብዛኛው በዝሙት የተጠቁ እና የሚተዳደሩ፣ ትዳራቸውን በየፍርድ ቤቱ የሚፈቱ፣ ለተለያዩ ሱሶች የተገዙና በመጠጥ ብዛት የሚሰክሩ፣ በስመ ክርስቲያን የሆኑ ነገር ግን በሕይወት የሌሉ ብዙ ናቸውና፡፡ ችግሩንም ለመፍታት ሁላችንም በጋራ ልንሠራ ይገባል፡፡ በተለያዩ መንገዶች ቃለ እግዚአብሔርን የሰማን፣ የተማርን፣ ለሌላውም መትረፍ የነበረብን ክርስቲያኖች ነበርን፡፡ ነገር ግን ለሥጋ በማድላት የተለያዩ ሰበቦችን በመደርደር፣ ኃላፊነትን፣ የእግዚአብሔርንና የቤተ ክርስቲያንን ውለታ በመርሳት አደራችንን መወጣት ያቃተን አለን፡፡ ይህ ከማኅበራዊ ሕይወት ውጪ ነውና ያለብንን አደራ እና ኃላፊነት በማሰብ ልንወጣ ይገባል፡፡

በፌስቡክ የትስስር ገጽ ያግኙን

Search Search

አዳዲስ ጽሑፎች

  • አብርሃም ርእየ ፫ተ እደወ፤ በዛቲ ዕለት ምሥጢረ ሥላሴ ዜነወ።
  • በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!
  • ቅዱስ ዮሐንስ መጥምቅ
  • ዘመነ ክረምት
  • “መሠረተ ሃይማኖት” የተባለ የልጆች መጽሐፍ የፊታችን እሑድ እንደሚመረቅ የስብከተ ወንጌል እና ሐዋርያዊ አገልግሎት ገለጸ
  • ደብረ ማርቆስ ማእከል 252 የግቢ ጉባኤ ተማሪዎችን አስመረቀ።
  • በዘንድሮው ዓመት ባሕር ዳር ዩኒቨርስቲ ካዘጋጃቸው 18 ሜዳሊያ ዋንጫውን ጨምሮ 14ቱ በግቢ ጉባኤያት ተማሪዎች የተወሰዱ መሆናቸው ተገለጸ
  • የግቢ ጉባኤ አባል (CGPA) 4.00 ነጥብ በማምጣት የዓመቱ የዋንጫ እና የወርቅ ሜዳሊያ ተሸላሚ ሆነ።
  • ማኅበረ ቅዱሳን እያስገነባ የሚገኘውን የልህቀት ማእከል የመጀመሪያ ዙር የፊኒሺንግ ሥራ ለማከናወን የገንዘብና የዐይነት ድጋፍ ማሰባሰብ መጀመሩን አስታወቀ
  • እንኳን ለእናታችን ለእመቤታችን ለቅድስተ ቅዱሳን ለድንግል ማርያም ሰኔ ጐልጐታና ሕንጸተ ቤተ ክርስቲያን (ለመጀመሪያ ጊዜ ቤተ ክርስቲያኗ ለታነጸበት) ክብረ በዓል በሰላምና በጤና አደረሰን አደረሳችሁ፡፡
  • የእንጅባራ ማእከል ላለፉት 4 ዓመታት ሲያስተምራቸው የቆዩ 200 ተማሪዎችን  አስመረቀ
  • ማኅበረ ቅዱሳን በመተከል ዞን ዳንጉር ወረዳ ለሚገኙ ተፈናቃዮች  አስቸኳይ የምግብ ግብዓቶች ድጋፍ አደረገ
  • የአዲስ አበባ ማእከል 500 የግቢ ጉባኤ ተማሪዎች መመረቃቸውን ገለጸ።
  • የወላይታ ሶዶ ማእከል ለ8 ወራት ያስተማራቸውን 45 የበገና ዘማርያንን አስመረቀ።
  •    ‘’ከመላእክት አለቆች አንዱ የሆነው ሚካኤል ሊረዳኝ መጣ።’’ (ት.ዳን. ፲ ፥፱)

የጽሑፎች ማውጫ – በወራት

© Mahibere Kidusan - All Rights Reserved. Website by MK-IT
  • Link to Facebook
Link to: መልእክተ ቅዱስ ፓትርያርክ Link to: መልእክተ ቅዱስ ፓትርያርክ መልእክተ ቅዱስ ፓትርያርክ Link to: የ38ኛው የመንበረ ፓትርያርክ አጠቃላይ የሰበካ መንፈሣዊ ጉባኤ የውሳኔ ሐሳብና የአቋም መግለጫ Link to: የ38ኛው የመንበረ ፓትርያርክ አጠቃላይ የሰበካ መንፈሣዊ ጉባኤ የውሳኔ ሐሳብና የአቋም መግለጫ የ38ኛው የመንበረ ፓትርያርክ አጠቃላይ የሰበካ...
Scroll to top