ማኅበረ ቅዱሳን በሰሜን አሜሪካ ሜኖሶታ ሁለት ከተሞች የኦሮምኛ ቴሌቪዥን ሥርጭት ጀመረ

ሚያዚያ 11 ቀን 2008 ዓ.ም

ከአሜሪካ ማእከል

ማኅበረ ቅዱሳን በሰሜን አሜሪካ ሜኖሶታ ውስጥ በሚገኙ በሚኖፖሊስ እና በቅዱስ ጳውሎስ /Minneapolis & Saint Paul/ ሁለት ከተሞች ከሚያዚያ 9 ቀን 2008 ዓ.ም ጀምሮ ሥርጭቱን ማስተላለፍ መጀመሩን የአሜሪካ ማእከል ገለጸ፡፡

የቴሌቪዥን ሥርጭቱ በየሳምንቱ እሑድ ከቀኑ 10፡00 ሰዓት /Sunday at 4:00 PM USA Central time/ በቻናል 75 የሚተላለፍ ሲሆን ምእመናን መርሐ ግብሩን እንዲከታተሉ ማእከሉ አስታውቋል፡፡

በተያያዘ ዜና በአሜሪካ የሜኖፖሊስ ማእከል ሚያዚያ 8 እና 9 ቀን 2008 ዓ.ም ጉባኤ ማካሔዱን የደረሰን መረጃ ያመለክታል፡፡