መስክርላት

ጥበብን በልክህ ሰፍታ ምታለብስህ፣
ሁሌም እንዲያምርብህ እንድትታይላት የምትለግስህ፣
ከማያልቅ ምንጯ ከጥልቅ ባሕሯ የምታስጎነጭህ፣
ያስከበረችህ ናት ተዋሕዶ እናትህ፣
በታናሽነትህ ደካማውን አንተን ታላቅ ያረገችህ፡፡

በደጇ መጣልን በቤቷ መውደቅን፣
እንድትመኝ ሁሌም በውስጧ መኖርን፡፡
ታሰማለች ድምጿን ትመለስላት ዘንድ፣
ከዘላለም ሕይወት ከሚለየው መንገድ፡፡
ስብዕና እንዲኖርህ ያልጎደለው ሰላም፣
ፈሩን ያለቀቀ ያልበረዘው ዓለም፡፡
እርሷን ተከተላት በትሕትና ሆነህ፣
ለታመምከው ለአንተ ለተጎሳቆልከው ፈውስ እንድትሆንህ፡፡

የኀላህን ዘመን የነበርክበትን፣
ክፉ ቀኖችህን ያሻገረችህን፡፡
እውነትን ሳትለቅ ለሁሉም ግለጣት፣
በእሷ መኖርህን በእሷ መክበርህን ሁሌ መስክርላት፡፡

  • ሳምራዊት ሰለሞን
    ከሐረማያ ዩኒቨርሲቲ ሐረር ጤናና ሕክምና ሳይንስ ግቢ ጉባኤ
0 replies

Leave a Reply

Want to join the discussion?
Feel free to contribute!

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *