መንፈሳዊነት
ኦርቶዶክሳዊነት ርትዕት ሃይማኖት፣ ጽኑ እምነት፣ መልካም ምግባርና መንፈሳዊ እውቀት በአንድነት የተዋሐዱበት፤ አርአያ እግዚአብሔርን አጽንቶ በሐዋርያዊ የሕይወት ተጋድሎ እግዚአብሔርን በግብር ወደ መምሰል የሚታደግበት ፍጹም ሰማያዊ ሕይወት በመሆኑ፤ አባላት በየትኛውም ቦታ፣ ጊዜና ሁኔታ በማሰብ፣ በመናገር እና በመሥራት/በተግባር በሚገለጽ ክርስቲያናዊ ሥነ ምግባር ታንጸው፣ ፍኖተ አበውን ተከትለው፣ በታማኝነት እና በፈሪሐ እግዚአብሔር ቤተ ክርስቲያንን በቅንነት ያገለግላሉ::
‹‹በራስህ አስተያየት ጠቢብ አትሁን›› (ምሳ. ፫፥፯)
በቅርብ ጊዜ ከተነሡት ፍልስፍናዎች አንዱና እጅግም የተስፋፋው የኢ-አማንያን አመለካከት ማለትም ‹‹ሃይማኖት የጦርነት ምንጭ ነው፤ ስለዚህ አያስፈልግም›› በሚል ክርስትናን እና ተዋሕዶ ሃይማኖትን በመንቀፍ ለቤተ ክርስቲያን መቃጠልና ለበርካታ ምእመናን ሞት መንሥኤም ሆኗል፡፡ ይህ የምዕራባውያን አስተሳሰብ የቤተ ክርስቲያንን ሕልውና መጋፋትና የተዋሕዶ ሃይማኖት አረንቋ ከሆነ ሰነባብቷል፡፡ ስለሆነም ከምን ጊዜውም የበለጠ ክርስቲያኖች በሃይማኖት እና በእምነት ሊጸኑ እንደሚገባ እንረዳለን፡፡
መጽሔተ ተልእኮ ዘማኅበረ ቅዱሳን
መጽሔተ ተልእኮ ዘማኅበረ ቅዱሳን መጽሔት በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ማኅበረ ቅዱሳን በሕዝብ ግንኙነት አገልግሎት የተዘጋጅ ነው፡፡ ከታች ያለውን ሊንክ በመጫን መጽሔቱን ያግኙ!
ዕረፍቱ ለሊቀ ነቢያት ሙሴ
እስራኤላውን በግብፅ ባርነት በተገዙበት ዘመን ፈርዖን እስራኤላውያን ወንድ ልጅ ሲወልዱ እንዲገደል በአዋጅ አስነገረ፡፡ የሙሴም እናት ልጇ በፈርዖን ትእዛዝ መሠረት እንዳይገደልባት ስለ ፈርዖን ትእዛዝ ፍራቻ ልጇን በቅርጫት አድርጋ ወንዝ ውስጥ ጣለችው፡፡ …
‹‹ዘመኑን ዋጁት›› (ኤፌ. ፭፥፲፮)
ዕለታት በወራት ተተክተው፣ አዲስ ዓመት ዘመንን ወክሎ በጊዜ ዑደት ውስጥ ያልፋሉ፡፡ ሰማይና ምድር እያፈራረቁ ቀንና ሌሊትን፣ ፀሐይንና ዝናብን ይለግሳሉ፡፡ ክስተቶቹም አልፈው ዳግም እስኪመለሱ በሌሎች ይተካሉ፤ የእግዚአብሔር ስጦታ ‹‹ጊዜ›› እንደዚሁ እስከ ዓለም ፍጻሜ ይቀጥላል፡፡
ሊቀ ሐመር
በባሕሩ ማዕበል፣ በአውሎ ነፋሱ ውሽንፍር ጊዜ ጭምር ሕይወቱን ለተሳፋሪዎች ደኅንነት አሳልፎ ይሰጣል፤ ሊቀ ሐመር፡፡ ከመርከቡ ርቀው፣ ስፍራቸውንም ትተው ጠፍተውም እንዳይሰጥሙ ይከታተላቸዋል፡፡ እርሱ ጠባቂያቸው ነውና፡፡ ያለ ሥጋት ተጉዘው ወደ ባሕሩ ዳርቻ እንዲደርሱም በሰላም ይመራቸዋል፡፡
ባሕረ ሀሳብ
የእስክንድርያ ዐሥራ ሁለተኛ ጳጳስ የነበረው ቅዱስ ድሜጥሮስ ባሕረ ሀሳብን ሲደርሰው የቤተ ክርስቲያን ዕውቀት ያልነበረው በግብርና ሥራ የሚተዳደር ሰው ነበር፡፡ ሆኖም ለዘመናት ቤተ ክርስቲያን በዚህ ሥርዓት የተመራችበትን የዘመን አቆጣጣር በመንፈስ ቅዱስ ተመርቶ ሊደርሰው ችሏል፤ ታሪኩም እንዲህ ነበር፡፡
ርእሰ ዐውደ ዓመት
እነሆ ለ፳፻፲፫ ዓ.ም. ዘመነ ማቴዎስ ዐውደ ዓመት እንደርስ ዘንድ የአምላካችን እግዚአብሔር ፈቃዱ ሆነ፤ ቅድስት ቤተ ክርስቲያንም በሥርዓቱ መሠረት የበዓላቱና የአጽዋማቱ መደብ የሚታወቅበትና የዘመናቱ ሂደት ተቀምሮ የሚታወጅበት ዕለት መስከረም አንድ ቀን ርእሰ ዐውደ ዓመትን ታከብራለች፡፡
«እውነት እላችኋለሁ፤ ሴቶች ከወለዱአቸው ወገን ከመጥምቁ ዮሐንስ የሚበልጥ አልተነሣም» (ማቴ.፲፩፥፲፩)
…ቅዱስ ዮሐንስ ታሥሮ ከጳጉሜን ፪ ቀን እስከ መስከረም ፪ ቀን በእስር ቤት ቆየ፡፡ ያሳሰረው ሔሮድስ አንቲጳስ መስከረም ሁለት ቀን የልደት በዓሉን ያከብር ነበር፡፡ በዚህ ዕለት የሆነውን ነገር ቅዱስ ማቴዎስ በወንጌሉ በምዕራፍ ፲፬ እንደሚከተለው አስፍሮታል፡፡…
በዓለ ቅዱስ ሩፋኤል
በወርኀ ጳጉሜን ከሚታሰቡ እና ከሚከበሩ በዓላት መካከል በየዓመቱ ጳጕሜን ፫ ቀን የሊቀ መላእክት የቅዱስ ሩፋኤል ዓመታዊ ክብረ በዓል በመላው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ አብያተ ክርስቲያናት በልዩ ልዩ መንፈሳዊ ሥነ ሥርዓት ይከበራል፡፡
በኦሮምያ ክልላዊ መንግሥት በክርስቲያኖች ላይ የተፈጸመውን ጥቃት አስመልክቶ ከማኅበረ ቅዱሳን የተሰጠ ማሳሰቢያ
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ሰሞኑን በኦሮምያ ክልላዊ መንግሥት በሚኖሩ በክርስቲያኖች ላይ የደረሰውን ጥቃት አስመልክቶ ላወጣችው መግለጫ የክልሉ መንግሥት ኮሚኒኬሽን ቢሮ የሰጠውን ማስተባበያ መንግሥት በድጋሚ እንዲያጤነው ለማሳሰብና የማኅበሩን አቋም ማሳወቅ አስፈላጊ ሆኖ በመገኘቱ ማኅበረ ቅዱሳን ይህን ማሳሰቢያ መስጠት አስፈላጊ ሆኗል፡፡