መንፈሳዊነት
ኦርቶዶክሳዊነት ርትዕት ሃይማኖት፣ ጽኑ እምነት፣ መልካም ምግባርና መንፈሳዊ እውቀት በአንድነት የተዋሐዱበት፤ አርአያ እግዚአብሔርን አጽንቶ በሐዋርያዊ የሕይወት ተጋድሎ እግዚአብሔርን በግብር ወደ መምሰል የሚታደግበት ፍጹም ሰማያዊ ሕይወት በመሆኑ፤ አባላት በየትኛውም ቦታ፣ ጊዜና ሁኔታ በማሰብ፣ በመናገር እና በመሥራት/በተግባር በሚገለጽ ክርስቲያናዊ ሥነ ምግባር ታንጸው፣ ፍኖተ አበውን ተከትለው፣ በታማኝነት እና በፈሪሐ እግዚአብሔር ቤተ ክርስቲያንን በቅንነት ያገለግላሉ::
በዓለ ፅንሰቱ ለእግዚእነ ወመድኃኒነ ኢየሱስ ክርስቶስ
የዓለም ቤዛ፣ የዓለም መድኃኒት፣ የሰው ልጆች አዳኝ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ሥጋን ተዋሕዶ ወደ ምድር ይመጣ ዘንድ የድኅነት ግብሩ የተፈጸመበት የምሥራች ቃል የተነገረበት እንዲሁም ከንጽሕት ቅድስት ድንግል ማርያም የተፀነሰበት ዕለት መጋቢት ፳፱ ታላቅ በዓል ነው፡፡ የነገረ ድኅነቱ የመፈጸሚያ ጅማሮ ይህ ዕለት የተቀደሰ በመሆኑም ቅድስት ቤተ ክርስቲያናችን ትዘክረዋለች፤ ታከብረዋለችም፡፡
ይቅርታ
ውድ የእግዚአብሔር ልጆች! እንዴት አላችሁ? ትምህርት እንዴት ነው? ትምህርት የምንፈልገውን ነገር ለማግኘት የሚደግፈንና በምድራዊ ኑሯችን ወደፊት ለመሆን የምንመኘውን ለማግኘት የምንጓጓበት መንገድ ነው! …ልጆች! የወላጆቻችሁ ምኞት ጎበዝ፣ ብልህ፣ አስተዋይና ታማኝ ስትሆኑ ለማየት ነው፡፡ መልካም! ለዛሬ የምንማማረው ባለፈው የጀመርነውን የክርስቲያናዊ ሥነ ምግባር ቀጣዩን ክፍል ‹‹ይቅርታ›› በሚል ርእስ ይሆናል፡፡ መልካም ቆይታ!
ኒቆዲሞስ
ቅዱስ ያሬድ ንብ የማትቀስመው አበባ እንደሌላት ሁሉን ቀስማ ያማረ የጣፈጠ ማር እንድትሠራ እርሱም ሐዲሳትን ከብሉያት እያስማማ ለጀሮ የሚስማማ ኅሊናን የሚመስጥ ድንቅ ዜማ ባዘጋጀልን መሠረት የዐቢይ ጾም ሰባተኛው ሳምንት ኒቆዲሞስ ተብሎ ይጠራል፡፡ ሊቁ “ኒቆዲሞስ ስሙ ዘሖረ ኀቤሁ ቀዲሙ ሌሊተ ወይቤሎ በጽሚት ረቢ ነአምን ብከ ከመ እምኀበ አብ መጽአከ ሖረ ኀቤሁ ዘስሙ ኒቆዲሞስ ወይቤሎ ለኢየሱስ ረቢ ሊቅ ንሕነ ነአምን ብከ ከመ እምኀበ አብ መጻአከ ከመ ትኩን መምሕረ ወበምጽአትከ አብራህከ ለነ ወሰላመ ጸጎከነ አንሥእ ኃይለከ ወነዓ አድኅነነ፤ አስቀድሞ በሌሊት ወደርሱ ይሔድ የነበረ ስሙ ኒቆድሞስ የሚባል ሰው በቀስታ “ሊቅ ሆይ ከአብ ዘንድ እንደመጣህ እናውቃለን” አለው። ኒቆዲሞስም ወደ እርሱ ሔደ፤ ረቢ ኢየሱስንም ሊቅ (አዋቂ) እንደሆንክ ለማስተማር ከአብ ዘንድም እንደመጣህ እኛ እናውቃለን፤ በምጽአትህም አበራህልን፤ ሰላምንም ሰጠኸን፤ ኃይልህን አንሳ፤ መጥተህም አድነን አለው” ይለናል። (ጾመ ድጓ)
የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ ከቤተ ክርስቲያን በውግዘት ተለይተው የነበሩትን የዐሥራ ሰባቱ አባቶች ውግዘት ማንሳቱን በመግለጫው አሳወቀ።
ቅዱስ ሲኖዶስ ከዚህ ቀደም ከቤተ ክርስቲያን ሥርዓተ ክህነት ውጭ በሆነ መንገድ በራሳቸው ሥልጣንና በይገባናል ስሞታ የኦሮሚያ ሲኖዶስ መሥርተናል በሚል ተልእኮ ሲንቀሳቀሱ ቢቆዮም በይቅርታ መመለሳቸውን ግንዛቤ ውስጥ በማስገባት ይህን ውሳኔ ማሳለፉን አስታውቋል፡፡
ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን አዲስ አበባ ሀገረ ስብከት የተሰጠ መግለጫ
በቅርቡ በተቋቋመው በኦሮሚያ ክልል ሸገር ከተማ አስተዳደር ውስጥ በቅድስት ኦርቶዶክሳዊት ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን፤ በአገልጋዮቿ እና በምእመናን ላይ እየተፈጸመ ያለውን ግፍ እና በደል አስመልክቶ ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን አዲስ አበባ ሀገረ ስብከት የተሰጠ መግለጫ።
“መኑ ውእቱ ገብር ኄር፤ የታመነ በጎ አገልጋይ ማን ነው?” (ቅዱስ ያሬድ)
ፈልፈለ ማኅሌት ቅዱስ ያሬድ በጾመ ድጓው እንዲህ እያለ ይዘምራል፤ “ገብር ኄር ወገብር ምእመን ገብር ዘአሥመሮ ለእግዚኡ፣ መኑ ውእቱ ገብር ኄር ወገብር ምእመን ዘይረክቦ እግዚኡ በምግባረ ሠናይ ወይሠይሞ ዲበ ኵሉ ንዋዩ ወካበ ይቤሎ እግዚአብሔር ገብር ኄር ወምእመን ዘበውኀድ ምእመነ ኮንከ ዲበ ብዙኅ እሠይመከ ባእ ውስተ ፍሥሓሁ ለእግዚእከ፤ጌታው በመልካም ሥራ የሚያገኘው በሐብቱ ሁሉ ላይ የሚሾመው የታመነ በጎ አገልጋይ ማን ነው? ዳግመኛም እግዚአብሔር አንተ የታመንክ በጎ አገልጋይ በጥቂቱ የታመንህ ስለኾንህ በብዙ እሾምሃለሁ ወደ ጌታህ ደስታ ግባ ይለዋል፡፡” (ጾመ ድጓ) ቅድስት ቤተ ክርስቲያን በዐቢይ ጾም ስድስተኛ ሳምንት ገብር ኄር ልጆቿን ስለ አገልግሎትና የአገልግሎት ዋጋ በስፋት የምታስተምርበት ሳምንት ነው።
ግብጻዊቷ ቅድስት ሣራ
ባለጸጋ ከሆኑ ግብጻዊ ወላጆቿ የተወለደቸው ቅድስት ሣራ በምንኩንስና ሕይወት የኖረች ተጋዳይ እንደነበረች ገድሏ ይናገራል፡፡ የመጋቢት ፲፭ (ዐሥራ አምስት) ቀን መጽሐፈ ስንክሳር እንደሚገልጸው ከልጅነት ጀምሮ በምንኩስና ሕይወት ቅንዓት ኖራለች፡፡ ወላጆቿ ክርስቲያናች ስለነበሩና ቅዱሳት መጽሐፍትን ማንበብና መጻፍ ስላስተማሯት በተለይም የመነኰሳትን ገድል ማንበብ ታዘወትር ነበር፡፡ በዚህም የተነሣ ከላይኛው ግብጽ ወደ ሚገኝ ገዳም በመሄድ ለረጅም ዓመታት ደናግልን ስታገለግል ኖሯለች፡፡
ታማኝነት
ውድ የእግዚአብሔር ልጆች! እንዴት አላችሁ? ታላቁ ዐቢይ ጾም እንዴት ነው? እንደ አቅማችሁ እየጾማቸችሁ ነው? የወላጆቻችሁ ድካማቸውና ክፍያቸው እናንተ ጎበዝ፣ ብልህ፣ አስተዋይና፣ ታማኝ ስትሆኑ ማየት ነውና በርቱ! ልጆች! ለዛሬ የምንማማረው ባለፈው የጀመርነውን ትምህርት የክርስቲያናዊ ሥነ ምግባር ቀጣዩን ክፍል “ታማኝነት” በሚል ርእስ ይሆናል፤ መልካም ቆይታ!
ዜና ዕረፍት
የብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርክ ልዩ ጽሕፈት ቤት እና የውጪ ግንኙነት መምሪያ የበላይ ኃላፊ እንዲሁም የድሬዳዋና የጅቡቲ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ ዶ/ር አቡነ አረጋዊ ከዚህ ዓለም ድካም ዐርፈዋል። ብፁዕነታቸው ለረጅም ጊዜ በሀገር ውስጥና ከሀገር ውጪ በሕክምና ሲረዱ ቆይተው ሊሻላቸው ባለመቻሉ ከዚህ ዓለም በሞተ ሥጋ ተለይተዋል።
በመንግሥትህ አስበኝ!
በሚያስፈራ ግርማህ በምጽዓት ቀን ስትገለጥ
በፊትህ የሚቆም ጠፍቶ ዓለም ሁሉ ሲንቀጠቀጥ
መልካሙን ዘር ከክፉው አበጥረህ ስትለያቸው
በፍርሃት ያርዳል የጽድቅ ፍሬ ለሌላቸው
ለእኔም ጨንቆኛል ዳግም የምትመጣበት
በደሌ ተቆጥሮ በሥራዬ የምመዘንበት