መንፈሳዊነት
ኦርቶዶክሳዊነት ርትዕት ሃይማኖት፣ ጽኑ እምነት፣ መልካም ምግባርና መንፈሳዊ እውቀት በአንድነት የተዋሐዱበት፤ አርአያ እግዚአብሔርን አጽንቶ በሐዋርያዊ የሕይወት ተጋድሎ እግዚአብሔርን በግብር ወደ መምሰል የሚታደግበት ፍጹም ሰማያዊ ሕይወት በመሆኑ፤ አባላት በየትኛውም ቦታ፣ ጊዜና ሁኔታ በማሰብ፣ በመናገር እና በመሥራት/በተግባር በሚገለጽ ክርስቲያናዊ ሥነ ምግባር ታንጸው፣ ፍኖተ አበውን ተከትለው፣ በታማኝነት እና በፈሪሐ እግዚአብሔር ቤተ ክርስቲያንን በቅንነት ያገለግላሉ::
የትምህርተ ሃይማኖት መቅድም
በሊቀ ጉባኤ አባ አበራ በቀለ አሚንሰ መሰረት ይእቲ ወካልአኒሃ ሕንጻ ወንድቅ እሙንቱ- እምነት መሠረት ናት ፤ ሌሎቹ ግን ሕንጻና ግንብ ናቸው:: በማለት ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ የሚያስገነዝበን እንደ ሕንጻና ግንብ ከሚቆጠሩት ከምግባርና ከትሩፋት ሁሉ በፊት የሃይማኖትን ቀዳሚነትና መሠረትነት ነው፡፡ መሠረት ሕንጻውን ሁሉ እንደሚሸከም እምነትም ምግባራትን ሁሉ ትይዛለች ፤ ሕንጻ ያለ መሠረት እንደማይቆም ምግባርም ያለ ሃይማኖት አይኖርም፡፡ […]
ሰባቱ ምስጢራተ ቤተክርስቲያን
በብፁዕ አቡነ ጎርጎርዮስ ካልዓይ ቤተ ክርስቲያን የመንፈስ ቅዱስ የጸጋው ግምጃ ቤት ስለሆነች መስቀል ላይ የተሰጠውን አምላካዊ ጸጋ በእምነት ለሚቀርቧት ሁሉ ታድላለች ፣ ትምህርቷን አምነው የተቀበሉ ሁሉ የዚህ ጸጋ ተካፋዮች ናቸው፡፡ ይህን ጸጋ ለምዕመናን የምታድልባቸውን መሳሪያዎች ምሥጢራት ትላቸዋለች፡፡ ሙሉውን እዚህ በመጫን ያንብቡ
ሰባቱ ምስጢራተ ቤተ ክርስቲያን
በሊቀ ጉባኤ አባ አበራ በቀለ ለሥጋ ሕይወታችን ልደት ፣ እድገትና ሌሎችም ነገሮች እንዳሉት መንፈሳዊ ሕይወታችንም እንደዚሁ ይኸንኑ የሚመስሉ ሁኔታዎች አሉት፡፡ በዚህ መሠረት አንድ ሰው መንፈሳዊ ልደትን የሚያገኘው በእምነትና በምሥጢረ ጥምቀት እንደሆነ እንረዳለን፡፡ ከዚህም ቀጥሎ ምሥጢረ ሜሮንና ምሥጢረ ቁርባን በተከታታይ ይፈጸማሉ፡፡ እነርሱም መንፈሳዊ ልደታችንንና እድገታችንን ከፍጹምና ያደርሱታል፡፡የአገልግሎትና የአንድነት ጸጋ የምናገኝባቸው ደግሞ ምሥጢረ ክህነትና ምሥጢረ ተክሊል […]
ክርስቲያናዊ ሕይወትና ምግባር (ሦስተኛ መጽሐፍ)
በሊቀ ጉባኤ አባ አበራ በቀለ አንድ ሰው የሚያንበትን እምነት ፣ የሚመራበትን ሕግ ፣ የሚያልመውን ተስፋና የሚወደውን ነገር ተከትሎ ከግቡ ለማድረስ ማድረግ ያለበትን በማድረግ ማድረግ የሌለበትን በመተው በነፃ ፈቃዱ ወስኖ በሙሉ ልቦናው በሙሉ ኃይሉ የሚያደርገው የውስጥና የውጭ መንፈሳዊ እንቅስቃሴ ፣ ጥረትና ትግል ነው፡፡ ሙሉውን እዚህ በመጫን ያንብቡ
ክርስቲያናዊ ሕይወትና ምግባር (ሁለተኛ መጽሐፍ)
በሊቀ ጉባኤ አባ አበራ በቀለ ሕገ እግዚአብሔርን መፈጸም ማለት ለአሥሩ ቃላት መታዘዝ ነው፡፡ አሥሩ ቃላት ደግሞ በፍቅር ትእዛዛት ይጠቃለላል፡፡ ሙሉውን እዚህ በመጫን ያንብቡ
የቤተ ክርስቲያን ታሪክ
በማኅበረ ቅዱሳን ትምህርት ክፍል ክርስቶስ በደሙ የመሰረታት ቤተ ክርስቲያን ምንም ፈተና ቢጸናባትም በእግዚአብሔር ኃይል ጠላቶቿን ድል እየነሳች በሐዋርያት ትምህርት ጸንታ ‹‹አሐቲ ቅድስት ቤተ ክርስቲያን›› በመባል አንድነቷን አጽንታ ቆይታለች፡፡ ሙሉውን እዚህ በመጫን ያንብቡ
ምስጢራተ ቤተ ክርስቲያን መግቢያ
በሊቀ ጉባኤ አባ አበራ በቀለ እግዚአብሔር የመረጣቸውን ሁሉ በሀብት ስቦ በረድኤት አቅርቦ ወደ ራሱ ይጠራቸዋል ፤ ያቀርባቸዋል፡፡ የተጠሩት ደግሞ በንዑሰ ክርስቲያንነት ደረጃ ቃለ እግዚአብሔርን እየሰሙ ከቆዩ በኋላ አዲስ ሕይወትን እንዲቀዳጁና ጸጋ መንፈስ ቅዱስን እንዲያገኙ የሚያበቃቸው ሌላ መንገድና ሥርዓት አስፈላጊ ስለሆነ ጌታ ራሱ አዘጋጅቶላቸዋል ፤ ሁላችንንም በዚህ መንገድ እንድንሄድ አዞናል፡፡ መንገድ የተባለውም ቃሉን ሰምቶ መፈጸምና […]
ነገረ ክርስቶስ በኦርቶዶክሳዊት ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን አስተምህሮ
በአቤል ሚካኤል ብርህት፣ ንጽህት፣ ጽድልት፣ የሆነች ቤተክርስቲያናችን ከምታስተምራቸው ትምህርቶች አንዱና ዋነኛው ነገረ ክርስቶስ ነው፡፡ በቤተክርስቲያን ትምህርት ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከቅድስት ሥላሴ አንዱ አካል ወልድ ሲሆን ከአብና ከመንፈስ ቅዱስ ጋር የተካከለ ሲሆን በኋላኛ ዘመን ከእመቤታችን ከድንግል ማርያም ከሥጋዋ ሥጋን ከነፍሷ ነፍስን ነስቶ ሰው ሆነ፡፡ ተጨማሪ ያንብቡ
ክርስቲያናዊ ሕይወትና ምግባር (አንደኛ መጽሐፍ)
በሊቀ ጉባኤ አባ አበራ በቀለ ክርስቲያናዊ ሕይወታችን ፍፁም የሚሆነው የዘልማዱን አኗኗር ትተን ከክርስቶስ ጋር አንድ ሁነን በእርሱ ቅዱስ መንፈስ ሱታፌ ኑሮን በእርሱና ስለ እርሱ ለእርሱ ብለን የምንሆነውና የምናደርገው የዘውትር ጥረትና መንፈሳዊ ተጋድሎ ነው፡፡ ክርስቲያናዊ ሕይወት ማለትም ትርጉሙ ይኸው ነው፡፡ ክርስቲያናዊ ምግባርም ወይም በጎ አድራጎት በዚሁ ትርጉም ውስጥ ቢጠቃለልም በተለየ መንገድ በክርስቶስ ሁነን ለሌሎች የምናደርገውን […]
ሥርዓተ ቤተክርስቲያን
በሊቀ ካህናት ክንፈ ገብርኤል አልታዬ ሥርዓት ማለት ‹‹ሠርዐ›› ሠራ ከሚለው የግእዝ ግስ የወጣ የምዕላድነት ዘር ያለው ስም ነው፡፡ ትርጉሙ ሕግ ደንብ አሠራር መርሐ ግብር ማለት ነው፡፡ ሙሉውን እዚህ በመጫን ያንብቡ