• እንኳን በደኅና መጡ !

ዜናዎች፣ ወቅታዊ ክንውኖች እና ልዩ ልዩ ይዘቶች

«ለራሱ ገንዘብ የሚያመቻች በእግዚአብሔር ዘንድ ግን ባለጠጋ ያልሆነ ሰው እንዲህ ነው»

ሦስተኛ እሑድ

 /ሉቃ. 12.21/
ጌታችን በይሁዳ አካባቢዎች እየተዘዋወረ ሲያስተምር ከህዝቡ አንድ ሰው ቀርቦ፡- «መምህር ሆይ ርስቱን ከእኔ ጋር እንዲካፈል ለወንድሜ ንገረው» አለው፡፡ ጌታችን ግን ወደዚህ ምድር የመጣው፣ ለመለኮታዊ /ሰማያዊ/ ዓላማና የሰውን ልጆች ለማዳን እንጂ በሰዎች ምድራዊ ኑሮ ገብቶ ሃብትን ለማከፋፈል ባለመሆኑ፣ ዳግመኛም እርሱ የመጣው ራስን ለሰው መስጠትን፣ ፍቅርንና አንድ መሆንን የምትሰብከውን ወንጌልን ለመስራት በመሆኑ «አንተ ሰው ፈራጅና አካፋይ እንዲሆን በላያችሁ ማን ሾመኝ?» በማለት ይህንን ሊያደርግ እንደማይወድ ከተናገረ በኋላ አጋጣሚውን በመጠቀም አብረውት ለነበሩት እንዲህ ብሎ አስተማራቸው፤ «የሰው ሕይወት በገንዘቡ ብዛት አይደለምና ተጠንቀቁ፤ ከመጎመጀትም ሁሉ ተጠበቁ»፡፡
St.Mary.JPG

ቅድስት ድንግል ማርያም

ጾመ ነቢያት

ዘመኑ ጾመ ነቢያት የተባለበት ምክንያት ነቢያት የተናገሩት ትንቢት ስለ ተፈጸመበት እንዲሁም በየዘመናቱ የተነሡ ነቢያት እግዚአብሔር ወደፊት ሊያደርግ ያሰበውን በእምነት ዓይን እያዩ ምሥጢር ተገልጦላቸው የራቀው ቀርቦ የረቀቀው ገዝፎ እየተመለከቱ ያዩትም መልካም ነገር እንዲደርስላቸው ስለ ጾሙ ስለ ጸለዩ ነው፡፡ ነቢያት ስለ ኢየሱስ ክርስቶስ መወለድ፣ ወደ ግብፅ ስለ መሰደድ፣ በባሕረ ዮርዳኖስ ስለመጠመቅ፣ በትምህርተ ወንጌል ጨለማውን ዓለም ስለ ማብራቱ፣ ለሰው ልጆች ድኅነት ጸዋትወ መከራ ስለመቀበሉና ስለ መሰቀሉ፣ ስለ ትንሣኤው፣ ስለ ዕርገቱና ስለ ዳግም ምጽአቱ ትንቢት ተናግረው አላቆሙም፤ ለአዳም የተሰጠው ተስፋ ተገልጦላቸው ለተናገሩት ትንቢት ፍፃሜ እንዲያደርሳቸው ፈጣሪያቸውን ተማፀኑትም እንጂ፡፡ በየዘመናቸው «አንሥእ ኃይለከ፣ ፈኑ እዴከ፤ ኃይልህን አንሳ እጅህንም ላክ» እያሉ ጮኹ፡፡ በጾምና በጸሎት ተወስነውም ሰው የሚሆንበትን ጊዜ በቀናት፣ በሳምንታት፣ በወራትና በዓመታት ቆጠሩ፡፡ ለምሳሌ ነቢዩ ኤርምያስ ስለ ሥጋዌው ትንቢት በተናገረ በ446 ዓመት ጌታችን ከእመቤታችን ከሥጋዋ ሥጋ ከነፍሷ ነፍስ ነስቶ ሰው ሆኗል፡፡

የድንግል ማርያም ስሞች

ከመንግስተአብ
 
ስም ለፈጣሪም ሆነ ለፍጡራን ለመጠሪያነት ያገለግላል፡፡ ይህም ስም አንዱን ከሌላው ለይቶ የሚያሳውቅ የፍቅር መግለጫ ነው፡፡ በጽሑፍም ሆነ በቃል ማስተላለፍ የሚቻለው በስም አማካኝነት ነው፡፡ በብሉይ ኪዳንም ሆነ በሐዲስ ኪዳን እግዚአብሔር ለሚወዳቸውና ለመረጣቸው ሰዎች ስም ያወጣ እንደ ነበር ሁሉ፤ ሰዎችም ያወጡ መጠሪያ ይሰጡ ነበር፡፡ ይህም ስም የሚሰየመው ወይም መጠሪያ ሆኖ የሚሰጠው እንዲሁ በዘፈቀደ ሳይሆን መሠረታዊ ምሥጢርና ትርጉም አለው፡፡ ሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያን «እስመ ስሙ ይመርህ ኀበ ግብሩ» በማለት ስም ግብርን ሁኔታን እንደሚገልጽ መሥክረዋል፡፡
St.Mary.jpg

የማኅበረ ቅዱሳን መተዳደሪያ ደንብ

በሐምሌ ወር 1994 ዓ.ም ቅዱስ ሲኖዶስ ያጸደቀው የማኅበረ ቅዱሳን መተዳደሪያ ደንብ   ሙሉውን እዚህ በመጫን ያንብቡ

Sinod.JPG

ቅዱስ ሲኖዶስ ሦስት መምሪያዎች በሊቃነ ጳጳሳት እንዲመሩ ውሳኔ ሰጠ

በሻምበል ጥላሁን

በሰኖዶሱ አባላት መካከል የተፈጠረው አለመግባባት በሰላም መፈታቱንም ገለጸ

ከጥቅምት 12 እስከ 19/ 2002 ዓ.ም መደበኛ ስብሰባውን ያደረገው የቅዱስ ሲኖዶስ ጉባኤ የሰንበት ትምህርት ቤት ማደረጃ መምሪያን ጨምሮ ሌሎች ሁለት መምሪያዎችን በበላይ የሚመሩ ሦስት ሊቃነ ጳጳሳትን በመምረጥና 10 ነጥቦችን የያዘ የአቋም መግለጫ በማውጣት ተጠ ናቀቀ፡፡

Sinod.JPG

Gambela_1.JPG

የጋምቤላ ርዕሰ መስተዳድር ኡሞድ ኡቦንግና የክልሉ ከፍተኛ ባለሥልጣናት ተጠመቁ

በ1 ነጥብ 8 ሚሊዮን ብር የተገነባው ቤተክርስቲያን ተመረቀ፡፡                  

በተከስተ አዳፍራቸው
የጋምቤላ ሕዝቦች ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት ርዕሰ መስተዳድርን ጨምሮ የክልሉ ፖሊስ ኮሚሽን ኮምሽነርና የካቢኔ ጉዳዮች ጽ/ቤት ሓላፊ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያንን እምነት ተቀብለው ተጠመቁ፡፡ በጋምቤላ ሀገረ ስብከት በአንድ ነጥብ ስምንት ሚሊዮን ብር ወጪ የተገነባው የደብረ መድኃኒት ቅድስት ኪዳነምሕረት ቤተክርስቲያን ተጠናቆ ቅዳሴ ቤቱም ተከብሯል፡፡Gambela_1.JPG

የመከሩ መሰብሰቢያ ጊዜው አሁን ነው

ለሁሉም ጊዜ አለው እንዳለ ጠቢቡ የሚሠራበትም ሆነ መሥራት የሚቻልበት ጊዜ አለው፡፡ ነገሮች ሁሉ የሚከናወኑበት፣ ቀና የሚሆኑበት፣ የሰው ልቡና ለበጎ ነገር የሚነሣሣበት ያለሙት የሚሠምርበት የዘሩት፣ የተከሉት ሁሉ የሚያፈሩበትና የሚጸድቅበት ጊዜ አለ፡፡

«በህልምም ተረድቶ ወደገሊላ ሀገር ሄደ፤……. ናዝሬት ወደምትባልም ከተማ መጥቶ ኖረ»

ሕዳር 6 ቀን እመቤታችን ጌታን ይዛ ከግብጽ /ከስደት/ ወደ ኢየሩሳሌም መመለሷ ይታሰባል፡፡ ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ ቀጥሎ ካለው የማቴዎስ ወንጌል ምንባብ በመነሳት ይህንን አስመልክቶ በማቴዎስ ወንጌል ትርጓሜው ላይ ያስተማረውን ትምህርት እናቀርባለን፡፡

ጉባኤው ባለ 26 ነጥብ የአቋም መግለጫና የውሳኔ ሐሳብ አሳለፈ

ለቤተክርስቲያን ልማት የላቀ አስተዋጽኦ ያበረከቱ ተሸለሙ

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን መንበረ ፓትርያርክ 28ኛው አጠቃላይ ሰበካ መንፈሳዊ ጉባኤ ባለ 26 ነጥብ የጋራ የአቋም መግለጫና የውሳኔ ሐሳብ በማቅረብ ተጠናቀቀ፡፡

በፌስቡክ የትስስር ገጽ ያግኙን

ስለ ማኅበረ ቅዱሳን መሰረታዊ መረጃዎች

ስያሜ

ማኅበረ ቅዱሳን እግዚአብሔር ያከበራቸው የነቢያት፣ የሐዋርያት፣ የጻድቃንና የሰማዕታት በአጠቃላይ የቅዱሳን ገድል፣ ትሩፋትና አማላጅነት የሚዘከርበት በመሆኑ ‹‹ማኅበረ ቅዱሳን›› የሚል ስያሜውን አግኝቷል፡፡

የማኅበሩ ርእይ

ቤተ ክርስቲያን ሁለንተናዊ የመሪነት ሚናዋን ስትወጣ ማየት

ተልእኮ

ለቤተ ክርስቲያን ተልእኮ መሳካት እና ለሕልውናዋ የሚተጋ፣ የተደራጀ ፣ ምሉዕ ኦርቶዶክሳዊ፤ ርቱዕ ዘመናዊ፤ ሁለገብ መሪ ትውልድ ማፍራት እና ማሰማራት

እሴቶች

  • መንፈሳዊነት

    ኦርቶዶክሳዊነት ርትዕት ሃይማኖት፣ ጽኑ እምነት፣ መልካም ምግባርና መንፈሳዊ እውቀት በአንድነት የተዋሐዱበት፤ አርአያ እግዚአብሔርን አጽንቶ በሐዋርያዊ የሕይወት ተጋድሎ እግዚአብሔርን በግብር ወደ መምሰል የሚታደግበት ፍጹም ሰማያዊ ሕይወት በመሆኑ፤ አባላት በየትኛውም ቦታ፣ ጊዜና ሁኔታ በማሰብ፣ በመናገር እና በመሥራት/በተግባር በሚገለጽ ክርስቲያናዊ ሥነ ምግባር ታንጸው፣ ፍኖተ አበውን ተከትለው፣ በታማኝነት እና በፈሪሐ እግዚአብሔር ቤተ ክርስቲያንን በቅንነት ያገለግላሉ::
  • አገልጋይነት

    የማኅበሩ አባላት አገልግሎትን የክርስቲያናዊ ሕይወታቸው መገለጫ አድርገው በመቀበል በበጎ ፈቃድ ሰማያዊውን ክብርና ጸጋ በመሻት፣ ምድራዊ ክብርና ውዳሴ ከንቱን ሳይፈልጉ፣ በትሕትና እና በክርስቲያናዊ ፍቅር በታማኝነት ያገለግላሉ::
  • የሐሳብ መሪነት

    ማኅበሩ ለቤተ ክርስቲያን ዘላቂ አገልግሎት የሚያስፈልጉ፣ ኦርቶዶክሳዊ እሳቤን የተከተሉና ዘመኑን የዋጁ የመሪነት ሐሳቦችን በማፍለቅ ከሚመለከታቸው የቤተ ክርስቲያን መሪዎች ጋር በመመካከር ይሠራል::
  • ተባባሪነት

    ማኅበሩ የቤተ ክርስቲያን አገልግሎት የሁሉም የቤተ ክርስትያን አካላት የወል ተግባር ነው ብሎ ያምናል:: በመሆኑም እንደየጉዳዩ አግባብነት ካላቸው ባለ ድርሻ እና አጋር አካላት ጋር በመግባባት፣ በመመካከር እና በቅንነት ለተልእኮ አንድነት ብዝኃ ጸጋን በማክበር አብሮ ይሠራል::
  • ሙያ አክባሪነት

    የማኅበሩ አባላት ባላቸው ልዩ ልዩ ሙያ /ዕውቀት/ ቤተ ክርስቲያንን ለማገልገል የተሰባሰቡ በመሆናቸው፣ በማኅበሩ አሠራሮች ሁሉ ከኦርቶዶክሳዊው ትምህርተ ሃይማኖት ጋር በማይጋጩ በእውነተኛ መረጃ ለሚደገፉ ሙያዊ ምክረ ሐሳቦች ተገቢውን ክብርና ቅድሚያ ይሰጣል:: በቤተ ክርስቲያንም ለመንፈሳዊ እና ለዘመናዊው (አስኳላ) ሙያ ተገቢው ክብር እንዲሰጥ ይሠራል::
  • ምክንያታዊ ሞጋችነት

    ማኅበሩ በእውነተኛ መረጃ ላይ ተመሥርቶ ቤተ ክርስቲያንን ከውስጥም ሆነ ከውጭ የሚፈትኑ አስተሳሰቦችን፣ አሠራሮችን፣ ልማዶችን እና ትርክቶችን በግልጽና በመንፈሳዊ ጥብዓት እና በእውነት እንዲሞገቱና መፍትሔ ላይ እንዲደረስ ይሠራል::
  • ተጠያቂነት

    የማኅበሩ አገልግሎት ግብ ሰማያዊ ዋጋ ማግኘት ስለሆነ ኀላፊነትን በአግባቡ አለመወጣት በእግዚአብሔር እና በሰዎች ዘንድ የሚያስጠይቅ በመሆኑ በየትኛውም እርከን ላይ ያለ አባል እና አመራር በማኅበሩ አሠራር መሠረት በተሰጠው ኀላፊነት ተጠያቂ ይሆናል፡፡

ዓላማዎች

  • የቤተ ክርስቲያን ተቋማዊ አስተዳደር፣ የአሠራር ሥርዐትና አስተሳሰብ፣ በቴክኖሎጂ እና በልዩ ልዩ መንገዶች በመደገፍ ዘመኑን ለዋጀ ጠንካራ አገልግሎት ማብቃት፤
  • የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተማሪዎችን ሙሉ ሰብእናን የሚገነባ ሥርዐተ ትምህርት በማስተማር ዘመኑን የዋጁ ምሉዕ ኦርቶዶክሳዊ የሆኑ በቤተ ክርስቲያን አስተዳደራዊ መዋቅር የሚያገለግሉ እንዲሁም በማኅበራዊ፣ በኢኮኖሚያዊ በፖለቲካዊ እና በሀገር አስተዳደር ጉዳዮች መሪ/ንቁ ተሳታፊ አገልጋዮችን ማፍራት እና ማሠማራት፤
  • የተተኪውን ትውልድ ምንጭ ለማጎልበት የሰ/ት/ቤቶችን አቅም በማጠናከር የሕጻናት እና የወጣቶችን የተተኪነት ሚና ማሳደግ፤
  • ኦርቶዶክሳዊ መንፈሳዊነትን በተግባር የሚገልጽ ቤተሰብ እና አንድነቱን የጠበቀ ኦርቶዶክሳዊ ማኅበረሰብ በመገንባት የተደራጀ እና የተናበበ አገልግሎት መስጠት፤
  • በተደራጀ እና ተደራሹን ማእከል ባደረገ መንገድ ስብከተ ወንጌልንና ሐዋርያዊ ተልእኮን ዘርፈ ብዙ በሆኑ መንገዶች በመላው ዓለም ማስፋፋት፤
  • በቤተ ክርስቲያን ላይ የሚነዙትን የርእዮተ ዓለም፣ የሐሰት ትርክቶች እና የአጽራረ ቤተ ክርስቲያንን እንቅስቃሴ ጥናት እና ምርምር ላይ ተመርኩዞ መሞገት እና የተሳሳቱትን በማረም፣ በጠንካራ የዕቅበተ እምነት አገልግሎት የቤተ ክርስቲያንን ሕልውና ማስጠበቅ፤
  • በተመረጡ ገዳማት እና አብነት ትምህርት ቤቶች የልኅቀት ማእከል እና የተለየ ክርስቲያናዊ ተልእኮ የሚፈጽሙ እንዲሆኑ የሚያስችል ሁለገብ የአእምሮ ልማት ድጋፍ ማድረግ፤
  • ማኅበሩ ዘመኑን የዋጀ ተቋማዊ የአሠራር ሥርዓት በመዘርጋት ተልእኮውን ማሳካት የሚችልበት አቅም መፍጥር ( በአመራር፣ በሰው ኃይል፣ በመንፈሳዊነት፣ በግንኙነት፣ በዕውቀት፣በልማት፣ በፋይናንስ፣ በቴክኖሎጂ)፤
  • ዓለም አቀፍ ግንኙነትና የትብብር አገልግሎትን መርሕ ያደረገ የኦርቶዶክሳውያን ኢኮኖሚያዊ፣ ማኅበራዊና ፖለቲካዊ ተሳትፎ ማሳደግ፣

አቡነ ጎርጎርዮስ ካልዕ
የሸዋ ሊቀ ጳጳስ ፲፱፻፴፪-፲፱፻፹፪ዓ.ም.

የማኅበሩ ህንጻ