መንፈሳዊነት
ኦርቶዶክሳዊነት ርትዕት ሃይማኖት፣ ጽኑ እምነት፣ መልካም ምግባርና መንፈሳዊ እውቀት በአንድነት የተዋሐዱበት፤ አርአያ እግዚአብሔርን አጽንቶ በሐዋርያዊ የሕይወት ተጋድሎ እግዚአብሔርን በግብር ወደ መምሰል የሚታደግበት ፍጹም ሰማያዊ ሕይወት በመሆኑ፤ አባላት በየትኛውም ቦታ፣ ጊዜና ሁኔታ በማሰብ፣ በመናገር እና በመሥራት/በተግባር በሚገለጽ ክርስቲያናዊ ሥነ ምግባር ታንጸው፣ ፍኖተ አበውን ተከትለው፣ በታማኝነት እና በፈሪሐ እግዚአብሔር ቤተ ክርስቲያንን በቅንነት ያገለግላሉ::
የትንሣኤ የማሕሌት ምንባብ 3 (ሉቃ.24፥1-13)
ከሳምንቱም በመጀመሪያዪቱ ቀን ያዘጋጁትን ሽቶ ይዘው እጅግ ማልደው ወደ መቃብሩ ሄዱ፤ ሌሎች ሴቶችም አብረዋቸው ነበሩ፡፡ ያቺንም ድንጋይ ከመቃብሩ ላይ ተንከባልላ አገኙአት፡፡ ገብተውም የጌታችን የኢየሱስን ሥጋ አላገኙም ስለዚህም ነገር የሚሉትን አጥተው ሲያደንቁ ሁለት ሰዎች ከፊታቸው ቆመው ታዩአቸው፤ ልብሳቸውም ያብረቀርቅ ነበር፡፡ ፈርተውም ፊታቸውን ወደ ምድር አቀረቀሩ፡፡ እነርሱም እንዲህ አሉአቸው፥ “ሕያዉን ከሙታን ጋር ለምን ትሹታላችሁ? በዚህ የለም፤ ተነሥቶአል፡፡ […]
ትንሣኤ /ለሕፃናት/
ሚያዝያ 6/2004 ዓ.ም.
የትንሣኤ የማሕሌት ምንባብ 1 (ማቴ.28፥1-ፍጻሜ )
የትንሣኤ የማሕሌት ምንባብ 2 (ማር.16፥1-ፍጻሜ )
በእሑድ ሰንበትም ማለዳ ተነሥቶ ሰባት አጋንንትን ላወጣላት ለማርያም መግደላዊት አስቀድሞ ታያት፡፡
እጅግ የተከበሩ የዓለም ሎሬት ሜትር አርቲስት አፈወርቅ ተክሌ አረፉ
ሚያዝያ 04፣ 2004ዓ.ም
ከጲላጦስ አደባባይ እስከ ሊቶስጥራ
{gallery count=1 width=350 height=300 counter=1 links=0 alignment=center animation=3000}Sekelete2{/gallery}
ቅዳሴን በካሴት ማስቀደስ ይቻላል?
ሚያዚያ 3/2004 ዓ.ም.
በዲ/ን ኅሩይ ባየ
እድሜ ለቴክኖሎጂ ይድረስና ድካምን የሚቀንሱ በርካታ የሥልጣኔ ውጤቶች እየተከሰቱ ነው፡፡ ከእነዚህ ውስጥ አንዱ መቅረጸ ድምጽ ሲሆን ያለፈን ለማስታወስ የለው ጠቀሜታ የጎላ ነው፡፡ መዝሙሮች ቅዳሴዎች፣ ትምህርቶች እና የአባቶች ምክር በካሴትና በሲዲ በምስልና በድምጽ እየተዘጋጁ የሚሰጡት አገልግሎት እጅግ ከፍ ያለ ነው፡፡
ጸሎት (ክፍል 2)
ሚያዚያ 3/2004 ዓ.ም.
በመ/ር ምሥጢረ ሥላሴ ማናየ
“አንትሙሰ ሶበት ጸልዩ ስመ ዝበሉ፡፡” ማቴ.6፥
እናንተስ በምትጸልዩበት ጊዜ እንዲህ በላችሁ ጸልዩ “አባታችን ሆይ በሰማያት የምትኖር ስምህ ይቀደስ መንግሥትህ ትምጣ ፈቃድህ በሰማይ እንደሆነ እንዲሁ በምድር ይሁን….
በዚህ የጸሎት ክፍል ክብር ምስጋና ይግባውና ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከ81 መጻሕፍት የተገኙ አምስት ቁም ነገሮችን አስተምሯል፡፡
ሃይማኖት
ተስፋ
ፍቅር
ትሕትና
ጸሎት
1. ሃይማኖት፡- ሃይማኖት ማለት በዐይናችን ያላየነውን አምላክ አባታችን ሆይ ሲሉ መኖር ነው ቀደም ሲል የነበሩ አበው ነቢያት ሲጸልዩ እግዚእነ አምላክነ ንጉሥነ እያሉ ይጸልዩ ነበር፡፡ ይህም ከግብርናተ ዲያብሎስ /ለዲያብሎስ ከመገዛት/ እንዳልዳኑ ለማጠየቅ ነው፡፡ እኛን ግን ከግብርናተ ዲያብሎስ ነጻ አውጥቻችኋለሁ ሲል አባታችን ሆይ ብላችሁ ጸልዩ ብሎ አስተማረን፡፡ “ልጆች እንደመሆናችሁ መጠን እግዚአብሔር አባ አባቴ ብላችሁ የምትጠሩትን የልጁን መንፈስ በልባችሁ አሳደረ” /ገላ.4፥6፣ ሮሜ.8፥15/፡፡ አባትነቱንም በሁለት ነገር ከምድራዊ አባት ለይቶታል፡፡
ማኅበረ ቅዱሳን የሥራ አመራር ጠቅላላ ስብሰባውን አካሔደ፡፡
02/08/2004 ዓ.ም.
በእንዳለ ደጀኔ
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን በሰንበት ትምህርት ቤቶች ማደራጃ መምሪያ ማኅበረ ቅዱሳን የ2004 ዓ.ም. የመጀመሪያውን ጉባኤ መጋቢት 22 እና 23 ቀን 2004 ዓ.ም. አካሒዷል፡፡
ጉባኤው የሥራ አመራሩ ባለፉት 6 ወራት ያከናወናቸውን የስብሰባና የውሳኔ ቃለ ጉባኤ ማጽደቅ፣ የሥራ አስፈጻሚ 6 ወር ክንውን ሪፖርት፤ በሀገር ውስጥ 42 እና ከሀገር ውጪ የሚገኙ 3 ማእከላትና 4 ግንኙነት ጣቢያዎች፣ የቅዱሳን መካናትና ልማትና ማኅበራዊ አገልግሎት ቦርድ፣ የልማት ተቋማት አስተዳደር ቦርድ የ6 ወር ክንውን ሪፖርት ገምግሞአል፡፡
የቃለ ዓዋዲው ክለሳ በውጭ ያለውን አገልግሎት ያካትት-
ሃያኛው መቶ ክፍለ ዘመን በኦርቶዶክሳዊት ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያናችን በርካታ ለውጦች የተስተናገዱበት ነበር፡፡ ከለውጦቹ ውስጥ ደግሞ ዋና ዋናዎቹ ሁለት ናቸው ማለት ይቻላል፡፡ የመጀመሪያው ለውጥ በውድ የመጣ ይልቁንም ለውጡ እውን ይኾን ዘንድ ከ0ኛው መቶ ክፍለ ዘመን ጀምሮ ነገሥታትና ኢትዮጵያውያን ሊቃውንት የተጋደሉለት ለውጥ ነው፡፡ ይኸውም የቤተ ክርሰቲያኗን አስተዳደር ለ1600 ዘመናት በቅብጥ ቤተ ክርስቲያን ጥላ ሥር እንዲቆይ ያደረገው ሊቃውንት መንበረ ጵጵስናውን ትንሽ ቆይቶም መንበረ ፕትርክናውን ተረክበው ዕውቀት መንፈሳዊ እየመገበች ያሳደገቻቸውን ቤተ ክርስቲያን መምራት የጀመሩበት የለውጥ ምዕራፍ ነው፡፡ ሁለተኛው ደግሞ ቤተ ክርስቲያኗ ለሀገር ለሕዝብ ለምትሰጠው አገልግሎት ዋጋ ይኾናት ዘንድ ከነገሥታት ተሰጥቷት የነበረው ርስት ጉልት ተነጥቆ «ራስሽን ቻይ» የተባለችበት የግድ ለውጥ ነው፡፡