መንፈሳዊነት
ኦርቶዶክሳዊነት ርትዕት ሃይማኖት፣ ጽኑ እምነት፣ መልካም ምግባርና መንፈሳዊ እውቀት በአንድነት የተዋሐዱበት፤ አርአያ እግዚአብሔርን አጽንቶ በሐዋርያዊ የሕይወት ተጋድሎ እግዚአብሔርን በግብር ወደ መምሰል የሚታደግበት ፍጹም ሰማያዊ ሕይወት በመሆኑ፤ አባላት በየትኛውም ቦታ፣ ጊዜና ሁኔታ በማሰብ፣ በመናገር እና በመሥራት/በተግባር በሚገለጽ ክርስቲያናዊ ሥነ ምግባር ታንጸው፣ ፍኖተ አበውን ተከትለው፣ በታማኝነት እና በፈሪሐ እግዚአብሔር ቤተ ክርስቲያንን በቅንነት ያገለግላሉ::
ልዩ የሕፃናት መርሐ ግብር ተዘጋጀ
ሐምሌ 10 ቀን 2004 ዓ.ም. በፍጹም ዓለማየሁ በ12 የአዲስ አበባ ሰንበት ትምህርት ቤቶች የጋራ ጥምረት እና በአፍሪካ ኅብረት ደብረ ምሕረት ቅዱስ ሚካኤል ካቴድራል ሰንበት ትምህርት ቤት አዘጋጅነት ለሕፃናት የሚሆን መርሐ ግብር ተዘጋጅቷል፡፡ መርሐ ግብሩ ከሐምሌ 12-15/2004 ዓ.ም. ለአራት ቀናት የሚካሄድ ሲሆን በሦስቱ የመጀመሪያ ቀናት “ዝክረ ቅዱሳን ሕፃናት በልሣነ ሕፃናት” በሚል መሪ ቃል በአስተናጋጅ ሰንበት ትምህርት […]
“ከሁሉ በላይ በምትሆን፤ ሐዋርያት በሰበሰቧት፤ በአንዲት፤ ቅድስት ቤተ ክርስቲያንም እናምናለን”
ሐምሌ 10 ቀን 2004 ዓ.ም.
ይህ አንቀጸ ሃይማኖት የጉባኤ ቁስጥንጥንያ አንቀጸ ሃይማኖት ነው፡፡ የእውነተኛዋ ቅድስት ቤተ ክርስቲያን መታወቂያ ትእምርትም ነው፡፡ ይህን አጉድሎ መገኘት የቤተ ክርስቲያንን ሕግና ሥርዐት ማፍረስ ብቻ ሳይሆን እምነትንም እንደማጉደል ይቆጠራል፡፡ እንዲህ ዐይነት ማንነታዊ ተክለ ቁመናን ገንዘብ ያደረገ ግለሰብም ሆነ ማኅበር ራሱን የክርሰቶስ አካልና አባል አድርጎ አለመቀበሉን ያሳየናል፡፡ በክርስቶስ ብቻ አምኖ በግለኝነት መኖር በቂ አይደለም፡፡ የክርስቶስ አካል በሆነችው ሐዋርያት በሰበሰቧት፣ በአንዲት፣ ቅድስት ቤተ ክርስቲያንም አምኖ አባል መሆን ሃይማኖታዊ ግዴታ ነው፡፡
ይሁንና ይህን አንቀጸ ሃይማኖት ያለ ዐውዱና ከተሸከመው መልእክት ውጪ በመለጠጥና አዲስ የትርጓሜ ቅርጽ በመስጠት በፕሮቴስታንታዊ ተሐድሶ መናፍቃን ቅላጼና ወዝ “ማኅበራት አያስፈልጉም” የሚል እና ራሱን “ጉባኤ አርድእት ዘኦርቶዶክስ ተዋሕዶ” ብሎ የሚጠራ የቤተ ክርስቲያናችን ሕመም የሆነ ቡድን ያለ ቤተ ክርስቲያኒቱ ዕውቅናና ይሁንታ ከሰሞኑ በመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት መሽጎና የተለያዩ ስብሰባዎችን እያካሄደ እንደሚገኝ ማረጋገጥ ችለናል፡፡
ቅዱስ ጴጥሮስ እና ቅዱስ ጳውሎስ
ዲያቆን ታደሰ ወርቁ እነዚህ ሁለት ቅዱሳን አባቶቻችን የቅድስት ቤተክርስቲያናችን አዕማድ ናቸው፡፡ በመሠረትነት በአጸኗት ቤተክርስቲያን ያላቸው የክብር ሥፍራ ላቅ ያለ ነው፡፡ ይህ የሆነው እንዲሁ አይደለም፡፡ ለቤተክርስቲያንና በቤተክርስቲያን የፈጸሙት አገልግሎት በዚህም የተቀበሉት ሰማዕትነት ነው፡፡ ቅዱሳት መጻሕፍትም ይህን መልካም የሆነውን ታሪካቸውን ለእኛ አርአያነት በሚሆን መልኩ ከትበውልናል፡፡ እኛም ለአርአርያነት በሚሆን መልኩ የእነዚህን ደጋግ ሁለት ቅዱሳን አባቶች ታሪክ፣ […]
ወርኃ ክረምት በቤተ ክርስቲያን ትምህርት (ዘመነ ክረምት)
ሐምሌ 4 ቀን 2004 ዓ.ም.
መብዐ ሥላሴ (ከጎላ ሚካኤል)
“ክረምት” የሚለው ቃል ከርመ፣ ከረመ ከሚለው የግእዝ ቃል የተገኘ ሲሆን ትርጓሜውም ወርሃ ዝናም፣ ወርኃ ነጎድጓድ፣ ዘመነ ባሕር፣ ዘመነ ነጎድጓድ፣ ዘመነ አፍላግ፣ ዘመነ ጠል፣ ዘመነ ደመና፣ ዘመነ መብረቅ… ማለት ነው፡፡(ጥዑመ ልሳን ካሳ ያሬድና ዜማው 1981 ዓ.ም ገጽ 53)
በዘመነ ክረምት ውኃ ይሰለጥናል፣ ውኃ አፈርን ያጥባል፣ እሳትን ያጠፋል፡፡ ሆኖም ግን በብሩህነቱ ከእሳት፤ በቀዝቃዛነቱ ከነፋስ፤ በእርጥብነቱ ከመሬት ጋር ተስማምቶ ከሦስቱ ባሕርያት ጋር ይኖራል፡፡ ይህ ዘመን ስለ ሥነ ፍጥረት ዘርዘር ባለ መልኩ የሚነገርበት ዘመን ስለሆነ ፍጡርን ከፈጣሪ መናን ከተመጋቢ ለይቶ የሚያሳይና የሚያሳውቅ ዘመን ነው፡፡
ዘመነ ክረምት፡- የዝናም፣ የዘርና የአረም ወቅት በመሆኑ ምድር በጠል ዝናም ትረካለች፡፡ ዕፅዋት አዝርዕትና አትክልት በቅለው፣ ለምልመው የሚያድጉበት፣ ምድር አረንጓዴ ለብሳ በሥነ ጽጌያት የምታሸበርቅበት፣ ወቅት ነው፡፡በመሆኑም በሃገራችን ብዙው የግብርና ሥራ የሚካሄደው በዚህ ጊዜ ነው፡፡
«ወደ እኔ ኑ፤ እኔም አሳርፋችኋለሁ» ማቴ. 11፥28
እግዚአብሔር ሁሉን አዘጋጅቶ በመጨረሻ ለፈጠረው ለሰው ልጅ ያላደረገለትና ያልሰጠው ነገር የለም፡፡ ሁሉን ከማከናወኑ ጋር የሰው ልጅ የሚያስፈልገውን ነገር በአባትነቱ ያውቃልና የሰው ልጅ በባሕርይው የሚያሻውን ነገር የሚያበጃጃት ገነት፣ የምትመቸውን ረዳት፣ የሚገዛቸውን ፍጥረታት ሁሉ ለሰው እንደሚገባ ሰጥቶታል፡፡ ከእነዚህ ተቆጥረው ከማያልቁ ሥጦታዎች አንዱ ደግሞ ዕረፍት ነው፡፡ «እግዚአብሔር የተናገረው ይህ ነው፤ ነገ ዕረፍት ለእግዚአብሔር የተቀደሰ ሰንበት ነው» ተብሎ እንደተጻፈ እግዚአብሔር ለሰው ልጆች ዕረፍት እንደሚያስፈልግ አውቆ የሰንበትን ቀን ሰጥቶአል /ዘጸ. 16.23/፡፡
«ሠርዐ ለነ ሰንበተ ለዕረፍተ ዚኣነ ፍስሓ ወሰላም ለእለ አመነ፤ ሰንበትን ለእኛ ዕረፍት ይሆን ዘንድ ሠራልን ደስታና ሰላም ለምናምን ሁሉ» እያልን በማለዳ ማመስገናችንም ከዚህ የመነጨ ነው፡፡ በባሕርይው ድካም የሌለበትና ዕረፍት የማይሻው አምላክ «ሰባተኛውን ቀን ባረከው፤ ቀደሰውም፤ ሊያደርገው ከፈጠረው ሥራ ሁሉ ዐርፎአልና» ተብሎ የተነገረው ከትንቢታዊ ትርጓሜው ባሻገር ሰንበት እግዚአብሔር ለሰው ልጅ ዕረፍት እንደሚያስፈልገው አውቆ ያዘጋጃት ማረፊያ መሆኗንና በተግባር «ዐረፈ» መባልን ፈጽሞ መስጠቱን ያስረዳል፡፡ ከሰውም አልፎ የምትታረስ መሬት እንኳን ዕረፍት እንድታደርግ ማዘዙም ለፍጥረቱ ዕረፍት የሚያስብ አምላክ ያሰኘዋል፡፡ እንግዲያስ የሰንበት ዕረፍት ለእግዚአብሔር ሕዝብ ቀርቶላቸዋል፡፡ ወደ ዕረፍቱ የገባ እግዚአብሔር ከሥራው እንዳረፈ እርሱ ደግሞ ከሥራው ዐርፎአልና /ዕብ. 4.9/፡፡
መራሒ
ማኅበረ ቅዱሳን የመኪና ስጦታ ተበረከተለት
ሰኔ 20 ቀን 2004 ዓ.ም. በእንዳለ ደጀኔ ማኅበረ ቅዱሳን የጀመረውን ዓለም አቀፍ መንፈሳዊና ማኅበራዊ አገልግሎት አጠናክሮ መቀጠል እንዲችል የሚያግዘው የመኪና ስጦታ ተበረከተለት፡፡ መኪናውን ለማኅበሩ ያበረከቱት ዶ/ር አንተነህ ወርቁና ዶ/ር ሰላማዊት እጅጉ ሲሆኑ ያዘጋጁትን ስጦታ በዶ/ር ሰላማዊት ወላጅ አባት በአቶ እጅጉ ኤሬሳ አማካኝነት አበርክተዋል፡፡ የመኪናውን ቁልፍ የተረከቡት የማኅበረ ቅዱሳን ም/ሰብሳቢ አቶ ታደሰ አሰፋ ‹‹ማኅበራችን ማኅበረ ቅዱሳን […]
በዓለ ልደቱ ለዮሐንስ መጥምቅ
ሰኔ 15 ቀን 2004 ዓ.ም በዘሚካኤል አራንሺ
እንኳን ለመጥምቀ መለኮት ቅዱስ ዮሐንስ በዓለ ልደት አደረሳችሁ::
የቅድስት ሥላሴ መንፈሳዊ ኮሌጅ 397 ደቀ መዛሙርትን አስመረቀ
በዲ/ን ዮሴፍ ይኲኖ አምላክ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን የቅድስት ሥላሴ መንፈሳዊ ኮሌጅ በቀን በማታና በርቀት ትምህርት ያስተማራቸውን ደቀመዛሙርት እሑድ ሰኔ 10 ቀን 2004 ዓ.ም ብፁዐን ሊቃነ ጳጳሳት በተገኙበት አስመረቀ፡፡ ኮሌጁ በቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ዩኒቨርሲቲ ሥር ሆኖ ከተቋቋመበት ከ1953 ዓ.ም ጀምሮ ለቅድስት ቤተክስቲያንና ለሀገራችን ለኢትዮጵያ ከፍተኛ አገልግሎት ያበረከቱ ደቀመዛሙርትን አሰልጥኖ ማውጣቱን የኮሌጁ ምክትል ዲን ዶክተር አባ […]
ሦስት አራተኛው መሬት