ye_mekina_setota

ማኅበረ ቅዱሳን የመኪና ስጦታ ተበረከተለት

ሰኔ 20 ቀን 2004 ዓ.ም.

በእንዳለ ደጀኔ

ማኅበረ ቅዱሳን የጀመረውን ዓለም አቀፍ መንፈሳዊና ማኅበራዊ አገልግሎት አጠናክሮ መቀጠል እንዲችል የሚያግዘው የመኪና ስጦታ ተበረከተለት፡፡


መኪናውን ለማኅበሩ ያበረከቱት ዶ/ር አንተነህ ወርቁና ዶ/ር ሰላማዊት እጅጉ ሲሆኑ ያዘጋጁትን ስጦታ በዶ/ር ሰላማዊት ወላጅ አባት በአቶ እጅጉ ኤሬሳ አማካኝነት አበርክተዋል፡፡


ye_mekina_setota

የመኪናውን ቁልፍ የተረከቡት የማኅበረ ቅዱሳን ም/ሰብሳቢ አቶ ታደሰ አሰፋ ‹‹ማኅበራችን ማኅበረ ቅዱሳን እግዚአብሔር ከዕለት ወደ ዕለት የሚያደር ግለት ነገሮች እየበዙ ነው፡፡ ይህን እንደምክንያት ልናየው እንችላለን ስለ ሁሉም ነገር ስጦታውን ያበረከቱትን ወንድምና እታችንን እናመሰግናለን ብለዋል፡፡›› አቶ ታደሰ አክለውም ‹‹የግንቦቱ የቅዱስ ሲኖዶስ ውሳኔ የማኅበረ ቅዱሳን አገልግሎት ለቤተ ክርስቲያን ወሳኝ መሆኑን የተረጋገጠበት ነው፡፡ የጎደለንን ነገር ስለሞላችሁልን እግዚአብሔር ይስጥልን›› ብለዋል፡፡


አቶ እጅጉ ኤሬሳ ስጦታውን በሰጡበት ወቅት ‹ልጆቼ የቤተ ክርስቲያንን አገልግሎት ዛሬ አይደለም የጀመሩት ፡፡ የጀመሩትን አገልግሎት እስከ ፍጻሜ እግዚአብሔር እንዲያጸናቸው በጸሎታችሁ አትርሱብኝ፡፡›› በማለት አሳስበዋል፡፡


በማኅበሩ ጽ/ቤት በተካሔደው የርክክብ ሥነ ሥርዓት ላይ የማኅበሩ የሥራ አመራር ጉባኤ አባላት፣ የሥራ አስፈጻሚ ጉባኤና የዶ/ር አንተነህ እህት ወ/ሮ ዘላለም ወርቁ ተገኝተዋል፡፡ የማኅበሩን አገልግሎት ለማገዝ በርካታ በጎ አድራጊዎች በተለያየ ጊዜያት ስጦታ ያበረክቱ ሲሆን ከዚህ ቀደም የአቶ ግርማ ዋቄ ባለቤት ወ/ሮ ውብዓለም ገብሬ የቤት መኪናቸውን ማበርከታቸው የሚታወስ ነው፡፡


ዶ/ር አንተነህና ዶ/ር ሰላማዊት ከጎንደር ዩኒቨርስቲ ተመርቀው ኑሮአቸውን በማሊ ያደረጉ ሲሆን ማኅበረ ቅዱሳን በቅዱሳን ገዳማትና አድባራት በሚያበረክተው አገልግሎት በጥሩ አርአያነት እያገለገሉ መሆናቸውን ለማወቅ ተችሏል፡፡