መንፈሳዊነት
ኦርቶዶክሳዊነት ርትዕት ሃይማኖት፣ ጽኑ እምነት፣ መልካም ምግባርና መንፈሳዊ እውቀት በአንድነት የተዋሐዱበት፤ አርአያ እግዚአብሔርን አጽንቶ በሐዋርያዊ የሕይወት ተጋድሎ እግዚአብሔርን በግብር ወደ መምሰል የሚታደግበት ፍጹም ሰማያዊ ሕይወት በመሆኑ፤ አባላት በየትኛውም ቦታ፣ ጊዜና ሁኔታ በማሰብ፣ በመናገር እና በመሥራት/በተግባር በሚገለጽ ክርስቲያናዊ ሥነ ምግባር ታንጸው፣ ፍኖተ አበውን ተከትለው፣ በታማኝነት እና በፈሪሐ እግዚአብሔር ቤተ ክርስቲያንን በቅንነት ያገለግላሉ::
የቅድስት ሥላሴ መንፈሳዊ ኮሌጅ የድኅረ ምረቃ መርሐ ግብር ጀመረ
ጥቅምት 29 ቀን 2005 ዓ.ም.
በዲ/ን ዮሴፍ ይኲኖ አምላክ
የግብጽ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን 118ኛውን ፓትርያርክ መረጠች
ጥቅምት 26 ቀን 2005 ዓ.ም.
በእንዳለ ደምስስ
የግብጽ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ለ40 ዓመታት ቤተ ክርስቲያኗን ሲመሩ የነበሩትንና በቅርቡ ያረፉትን ፓትርያርክ ብፁዕ አቡነ ሺኖዳ ሣልሳዊን ለመተካት 118ኛውን ፓትርያርክ እሑድ ጥቅምት 25 ቀን 2005 ዓ.ም. በታላቅ ሥነ ሥርዓት መረጠች፡፡
ቅድስት ቤተ ክርስቲያን በጎቿን ይዛ እንድትዘልቅ …
ጥቅምት 26 ቀን 2005 ዓ.ም.
በየዓመቱ በጥምቀት ወር በቅድስት ቤተ ክርስቲያን የአስተዳደርና ዘርፈ ብዙ አገልግሎት ላይ የሚመክረው አጠቃላይ የሰበካ መንፈሳዊ ጉባኤ ለሠላሳ አንደኛ ጊዜ ተካሂዷል፡፡ በዚህ ጉባኤ ላይ የእናት ቤተ ክርስቲያናቸውን የአገልግሎት ጥሪ የተቀበሉ ምሁራን ልጆቿ፤ በልዩ ልዩ ርእሰ ጉዳዮች ላይ ያተኮሩ ጥናት ጽሑፎቻቸውን አቅርበው ውይይት ተደርጎባቸዋል፡፡ በእንደዚህ ዓይነቱ ታላቅ ጉባኤ ላይ፤ ለቅድስት ቤተ ክርስቲያን ሁለንታዊ አገልግሎት መቃናት የሚበጁ፣ በየሙያ ዘርፉ ዕውቀትና ልምድ ባካበቱ ምሁራን ልጆቿ የሚቀርቡ የጥናት ጽሑፎችና የሚካሄዱ ውይይቶች፤ እናት ቤተ ክርስቲያን ትውልዱን ይዛ ዘመኑን እየዋጀች ጸንታ እንድትቀጥል በማድረግ ረገድ ጠቀሜታቸው የጎላ ነው፡፡
በማኅበረ ቅዱሳን የአርባ ምንጭ ማእከል 14ኛውን ጠቅላላ ጉባኤ እየተካሄደ ነው
ጥቅምት 24 ቀን 2005 ዓ.ም.
ከአርባ ምንጭ ማዕከል
በማኅበረ ቅዱሳን የአርባ ምንጭ ማእከል ከጥቅምት 23-25ቀን 2005 ዓ.ም 14ኛውን ጠቅላላ ጉባኤ በመካሔድ ላይ ነው ፡፡ በመክፈቻ መርሐ ግብሩ ላይ ከሀገረ ስብከት የመምሪያ ሓላፊዎች፣ በአርባ ምንጭ ከተማ የሚገኙ የአድባራት አስተዳዳሪዎች እና ሰበካ ጉባኤያት፣ የሰንበት ትምህርት ቤት ተወካዮች ፤ የ16 ወረዳ ማእከላት እና 3 ግንኙነት ጣቢያዎች ፤ የ10 ግቢ ጉባኤያት ተወካዮች እና ጥሪ የተደረገላቸው ተጋባዥ እንግዶች ተገኝተዋል፡፡
የአዲስ አበባ ማእከል 18ኛ መደበኛ ጠቅላላ ጉባኤ ተካሄደ፡፡
ጥቅምት 22 ቀን 2005 ዓ.ም.
በእንዳለ ደምስስ
የአዲስ አበባ ማእከል 18ኛ ጠቅላላ ጉባኤ ከጥቅምት 17-18 ቀን 2005 ዓ.ም. በጠቅላይ ቤተ ክህነት ስብከተ ወንጌል አዳራሽ ለሁለት ቀናት ተካሄደ፡፡
መርሐ ግብሩ በመንበረ ልዑል ቅዱስ ማርቆስ ቤተ ክርስቲያን ልዑካን ጸሎተ ወንጌል በማድረስ በብፁዕ አቡነ ዮሴፍ የባሌ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ቡራኬና ጸሎት ተጀምሯል፡፡
የጥቅምቱ ቅዱስ ሲኖዶስ ጉባኤ ተጠናቀቀ
ጥቅምት 21 ቀን 2005 ዓ.ም.
በዲ/ን ዮሴፍ ይኲኖ አምላክ
በፍትሕ መንፈሳዊ አንቀጽ 5 ቁጥር 164 በተደነገገው መሠረት ጥቅምት 11 ቀን 2005 ዓ.ም. ጀምሮ ለአሥር ቀናት ያህል በ17 አጀንዳዎች ላይ ሲነጋገር የሰነበተው የቅዱስ ሲኖዶስ ምልአተ ጉባኤ አስፈላጊ ናቸው ያላቸውን ውሳኔዎችን በማስተላለፍ ዛሬ ከቀትር በፊት ተጠናቀቀ፡፡
ባለፈው ዓመት የተከናወነውን ሥራ ለመገምገምና የወደፊቱንም እቅድ ለመንደፍ እንዲችል ከየአህጉረ ስብከቱ ጽ/ቤቶች የቀረቡለትን ሪፓርቶች አዳምጦ አስፈላጊውን መመሪያ የሰጠው ቅዱስ ሲኖዶስ በሰሜን አሜሪካ ከሚገኙት አባቶች ጋር የተጀመረው የእርቀ ሰላም ድርድር ተጠናክሮ ይቀጥል ዘንድ ውሳኔ አሳልፏል፡፡
ሊቀ ጉባኤ ኀይለ ማርያም ዐረፉ
ጥቅምት 20 ቀን 2005 ዓ.ም.
በቀሲስ ለማ በሱፍቃድ
ስርጭቱን ለማስቀጠል ጥረቶች እየተደረጉ መሆኑ ተገለጠ፡፡
ጥቅምት 19 ቀን 2005 ዓ.ም. በዲ/ን ዮሴፍ ይኲኖ አምላክ በኢ.ቢ.ኤስ ቴሌቪዥን አማካኝነት ከጥቅምት 4 ቀን 2005 ዓ.ም. ጀምሮ ይሠራጫል በሚል በምእመናን ዘንድ በጉጉት ሲጠበቅ የነበረው የማኅበሩ የቴሌቭዥን መርሐ ግብር የኢ.ቢ.ኤስ ጣቢያ ከጥቂት ጊዜያት ወዲህ ሙሉ ሥርጭቱ በመቋረጡ የተነሣ በታሰበው ጊዜ ለመጀመር አልተቻለም፡፡ ሆኖም የኢ.ቢ.ኤስ ሓላፊዎች በገለጹት መሠረት ጣቢያው እንደገና ሥርጨቱን ለማስጀመር ከፍተኛ እንቅስቃሴ እየተደረገ ሲሆን […]
፬ቱ ሆሄያት
ጥቅምት 19 ቀን 2005 ዓ.ም/
በዲ/ን ኅሩይ ባየ
የቅዱስ ሲኖዶስ የአራት ቀናት ውሎና ውሳኔዎች
ጥቅምት 15 ቀን 2005 ዓ.ም.
በእንዳለ ደምስስና
በዲ/ን ዩሴፍ ይኲኖ አምላክ
የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ለአስተዳደር እንዲመች በአራት አህጉረ ስብከት ተከፈለ፡፡
ጥቅምት 11 ቀን 2005 ዓ.ም. በመንበረ ፓትርያርክ ቅድስተ ቅዱሳን ማርያም ገዳም በተካሔደው ሥርዓተ ጸሎት የተከፈተው የቅዱስ ሲኖዶስ ምልአተ ጉባኤ ባሳለፍናቸው አራት ቀናት በስድስት ጠቃሚና ዋና ዋና አጀንዳዎች ላይ ተወያይቶ አስፈላጊ ናቸው ያላቸውን ውሳኔዎች አሳልፏል፡፡