መንፈሳዊነት
ኦርቶዶክሳዊነት ርትዕት ሃይማኖት፣ ጽኑ እምነት፣ መልካም ምግባርና መንፈሳዊ እውቀት በአንድነት የተዋሐዱበት፤ አርአያ እግዚአብሔርን አጽንቶ በሐዋርያዊ የሕይወት ተጋድሎ እግዚአብሔርን በግብር ወደ መምሰል የሚታደግበት ፍጹም ሰማያዊ ሕይወት በመሆኑ፤ አባላት በየትኛውም ቦታ፣ ጊዜና ሁኔታ በማሰብ፣ በመናገር እና በመሥራት/በተግባር በሚገለጽ ክርስቲያናዊ ሥነ ምግባር ታንጸው፣ ፍኖተ አበውን ተከትለው፣ በታማኝነት እና በፈሪሐ እግዚአብሔር ቤተ ክርስቲያንን በቅንነት ያገለግላሉ::
የሕፃኑ የኢየሱስ ልደት /ለሕፃናት/
ታኅሣሥ 26 ቀን 2005 ዓ.ም.
ከወልደ ኢየሱስ /ቤካ ፋንታ/
ልጆችዬ እንደምን ሰነበታችሁ? ዛሬ ስለ ታላቁ ሕፃን ልደት የምነግራችሁ ነገር አለና በማስተዋል ተከታተሉኝ እሺ፡፡ ጎበዞች!
የዛሬ ሁለት ሺ ዓመት ገደማ ነው፡፡ በኢየሩሳሌም ሀገር ንጉሡ ሄሮድስ ሕዝቡን ሁሉ ቤተልሄም ወደምትባል ከተማ ጠራቸው፡፡ እመቤታችንም በዚያ ጊዜ የአሥራ አምስት/15/ ዓመት ልጅ ሆኖ በሚጠብቃት በአረጋዊው /በሽማግሌው/ ዮሴፍ ቤት ትኖር ነበር፡፡ እመቤታችን ድንግል ማርያም ሕፃኑን ኢየሱስ ክርስቶስን ፀንሳ ልትወልድ ደርሳ ሳለ ወደ ቤተልሄም ከተማ ከአረጋዊው ጠባቂዋ ዮሴፍና ከቅድስት ሰሎሜ ጋር ሄደች፡፡
“ወብዙኀን ይትፌሥሑ በልደቱ በመወለዱም ብዙዎች ደስ ይላቸዋል” ሉቃ.1፥14
ታኅሣሥ 25 ቀን 2005 ዓ.ም.
ዲ/ን ዮሴፍ ይኲኖ አምላክ
በስልታዊ ዕቅድ ዙሪያ የግንዛቤ ማስጨበጫ ተሰጠ
ታኅሣሥ 22 ቀን 2005 ዓ.ም.
በእንዳለ ደጀኔ
ማኅበረ ቅዱሳን ከ2005 ዓ.ም – 2008 ዓ.ም ድረስ የሚተገበረውን የ4 ዓመት ስልታዊ ዕቅድ ዙሪያ በ6 ማእከላት ማስተባበሪያ አማካኝነት ለሁሉም ማእከላት የግንዛቤ ማስጨበጫ ምክክር መሰጠቱ ተገለጸ፡፡
እኛ የምናመልከው አምላክ ኪሚነደው ከእሳቱ እቶን ያድነን ዘንድ ይችላል፡፡ ት.ዳን.3፥17
ታኅሣሥ 18 ቀን 2005 ዓ.ም.
በዲ/ን ኀይለ ኢየሱስ ቢያ
የጥናትና ምርምር ማእከሉ ያዘጋጀው የጥናት ጉባኤ ተራዘመ
ታኅሣሥ 17 ቀን 2005 ዓ.ም. በማኅበረ ቅዱሳን የጥናትና ምርምር ማእከል ታኅሣሥ 20 ቀን 2005 ዓ.ም. “በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የፓትርያርክ ምርጫና የአባቶች እርቀ ሰላም” በሚል መሪ ቃል አዘጋጅቶት የነበረው የጥናት ጉባኤ ላልተወሰነ ጊዜ የተራዘመ ሲሆን የሚካሄድበትን ጊዜ ወደፊት የምናሳውቅ መሆኑን እንገልጻለን፡፡
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን እና የግብፅ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን የልምድ ልውውጥ አደረጉ
ታኅሣሥ 17 ቀን 2005 ዓ.ም.
በዲ/ን ኅሩይ ባየ
ከታኅሣሥ 11-15 ቀን 2005 ዓ.ም. ለአምስት ተከታታይ ቀናት የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን እና የግብፅ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን የልምድ ልውውጥ አደረጉ፡፡ የልምድ ልውውጡ የተከናወነው በመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ስብከተ ወንጌል አዳራሽ ሲሆን በአምስቱ ዕለታት በየቀኑ እስከ አንድ ሺሕ ለሚሆኑ የተለያዩ የቤተ ክርስቲያን አገልጋዮች መካፈላቸውን ለማወቅ ተችሏል፡፡
ሥልጠናው የአቋም መግለጫ በማውጣት ተጠናቀቀ
ታኅሣሥ 17 ቀን 2005 ዓ.ም.
በእንዳለ ደምስስ
ማኅበረ ቅዱሳን ከታኅሣሥ 6-11 ቀን 2005 ዓ.ም. ከ65 በላይ ለሚሆኑ የገዳማት አበመኔቶች፣ እመምኔቶችና ተወካዮች “የቤተ ክርስቲያንን ተልእኮ ለማሳካት የገዳማት ድርሻ” በሚል መሪ ቃል የግማሽ ቀን ዐውደ ጥናትና በዩኒቨርስቲ ምሁራን፤ በቅርስ ጥበቃ ባለሥልጣን፣ በጠቅላይ ቤተ ክህነት የገዳማት መምሪያ እንዲሁም በተጋባዥ ምሁራን ለአምስት ቀናት ሲሰጥ የቆየው ሥልጠና ተጠናቀቀ፡፡
ከልቼ ቤተመንግሥት እስከ ታዕካ ነገሥት ኢየሱስ
ታኅሣሥ 15 ቀን 2005 ዓ.ም.
በመ/ር ሳሙኤል ተስፋዬ
ዳግማዊ ዐፄ ምኒልክ ከአባታችው ከሸዋው ንጉሥ ኃይለ መለኮት ሣህለ ሥላሴና ከእናታቸው ወይዘሮ እጅጋየሁ ለማ አድያም ነሐሴ ፲፪ ቀን ፲፰፻፴፮ ዓ.ም. ደብረ ብርሃን አካባቢ አንጎለላ ከሚባል ሥፍራ ተወልደው፤ በአንጎለላ መቅደላ ኪዳነ ምሕረት ቤተ ክርስቲያን ክርስትና ተነሡ። አያታቸው ንጉሥ ሣህለ ሥላሴ የምኒልክን መወለድ ሲሰሙ “ምን ይልህ ሸዋ” በሉት ብለው ስም አወጡ። እሳቸው “…ምኒልክ በሚል ስም የሚነግሥ ንጉሥ ኢትዮጵያን ታላቅ ያደርጋታል” የሚል ትንቢት ስለነበር ‘ምኒልክ’ የኔ ስም ነው ብለው ነበር። ሆኖም፣ በህልማቸው ከልጁ ጋር አብረው ቆመው ከሳቸው ጥላ የልጁ ጥላ በልጦ፤ በእግር የረገጡትን መሬት ሲያለካኩ እሳቸው ከረገጡት ልጁ የረገጠው ረዝሞ አዩ። ከዚህ በኋላ “ምኒልክ የኔ ስም አይደለም። የሱ ነው። ስሙን ምኒልክ በሉት” ብለው አዘዙ። ጳውሎስ ኞኞ “አጤ ምኒልክ” በተባለው መጽሐፍ ።
ሁሉን መርምሩ መልካሙን ያዙ ፩. ተሰ. ፭፥፳
ታህሣሥ 6 ቀን 2005 ዓ.ም ምሽት ላይ በአሜሪካ ድምፅ ሬዲዮ የአማርኛ ፕሮግራም ዲ/ን ዓባይነህ ካሴ የተሰጡት ቃለ ምልልስ ማኅበሩን የማይወከል መሆኑን ስለማሳወቅ
በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ። አሜን። በማኅበረ ቅዱሳን ያላቸውን ሓላፊነት በመጥቀስ ዲ/ን ዓባይነህ ካሴ ታህሣሥ 6 ቀን 2005 ዓ.ም ምሽት ላይ በአሜሪካ ድምፅ ሬዲዮ የአማርኛ ፕሮግራም ለቃለ ምልልስ ቀርበው በወቅታዊው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ጉዳዮች ላይ ሓሳብ መስጠታቸው ይታወሳል። ማኅበረ ቅዱሳንን በመወከል ለመገናኛ ብዙኃን መግለጫም ሆነ ቃለ ምልልስ መስጠት የሚችሉት የማኅበሩ ሰብሳቢ […]