• እንኳን በደኅና መጡ !

ዜናዎች፣ ወቅታዊ ክንውኖች እና ልዩ ልዩ ይዘቶች

DSC09260

የምርጫው ሂደት በሰላም ይጠናቀቅ ዘንድ ሁሉም በጸሎት እንዲያስብ ተጠየቀ

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የ6ኛ ፓትርያርክ አስመራጭ ኮሚቴ የካቲት 8 ቀን 2005 ዓ.ም. በጠቅላይ ቤተ ክህነት በሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ ለፓትርያርክነት እጩ ሆነው የሚቀርቡ ጳጳሳትን ለመምረጥ ካህናትና ምእመናን ጥቆማ እንዲያደርጉ ከየካቲት 1 – 8 ቀን 2005 ዓ.ም. የሰጠው የጊዜ ገደብ መጠናቀቁን አስታወቀ፡፡

አስመራጭ ኮሚቴው በአንድ ሳምንት ውስጥ አከናወንኳቸው ያላቸውን ሥራዎች ባቀረበበት በዚሁ መግለጫ በርካታ ምእመናን ለቤተ ክርስቲያኒቱ 6ኛ ፓትርያርክ ሊሆኑ ይገባቸዋል ያሉትን አባት በአካል በመቅረብ እንዲሁም በፋክስ መልእክት በመላክ ጥቆማ መስጠታቸውን ገልጧል፡፡ ከካህናትና ምእመናን የተገኘው ጥቆማም ለአስመራጭ ኮሚቴው በግብአትነት የሚያገለግል ሲሆን ከየካቲት 9 -14 ቀን 2005 ዓ.ም. በወጣው የፓትርያርክ ምርጫ ሕገ ደንብ መሠረት አስመራጭ ኮሚቴው ለይቶ ከሦስት ያላነሱ ከአምስት ያልበለጡ እጩ ፓትርያርኮችን የካቲት 16 ቀን 2005 ዓ.ም. ለቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ እንደሚያቀርብ መግለጫው አመልክቷል፡፡ የምርጫው ሂደት በሰላም ይጠናቀቅ ዘንድም ብፁዐን ሊቃነ ጳጳሳት ፤ ካህናትና ምእመናን እግዚአብሔርን በጸሎት እንዲጠይቁ ኮሚቴው አሳስቧል፡፡

በጋዜጣዊ መግለጫው ላይ አስመራጭ ኮሚቴው ከጋዜጠኞች ለቀረቡላቸው ጥያቄዎችም ምላሾችንም ሰጥተዋል፡፡

ከጋዜጠኞች ከቀረቡት ጥያቄዎች መካከል ምርጫው ከሌሎች ተጽእኖ ምን ያህል የፀዳ ነው? የሚለውን ለቀ ማዕምራን ፋንታሁን ሙጬ የአስመራጭ ኮሚቴው ጸሐፊ ምላሽ የሰጡ ሲሆን አስመራጭ ኮሚቴው ከሌሎች አካላት ተጽእኖ የጸዳና ራሱን ችሎ የተሰጡትን ኃላፊነቶች በመወጣት ላይ እንደሚገኝ ገልጸዋል፡፡  የአኀት ቤተ ክርስቲያንና የሲቪክ ማኅበራት ምርጫውን ለመታዘብ ይገኛሉ? የሚለውን ሲመልሱም ከአኀት ቤተ ክርስቲናት፤ ከአለም አብተ ክርስቲናት ምክር ቤት፤ ከአፍሪካ አብያተ ክርስቲያናት ምክር ቤት፤ ከታዋቂ አገር ሽማግሌዎችና ከመንግስት አካላት በታዛቢነት እንደሚገኙ አብራርተዋል፡፡

በስፋት ጥቆማ እየሰጡ የሚገኙት የአዲስ አበባ ካህናትና ምእመናን ናቸው፡፡ ሌሎቹ አህጉረ ስብከቶችስ? በሚል ለቀረበው ጥያቄም ሲመልሱ “በርቀት ምክንያት በአካል መቅረብ ያልቻሉ ጥር 30 ቀን 2005 ዓ.ም. አስመራጭ ኮሚቴው ባወጣው መግለጫ ላይ ሁለት ፋክስ ቁጥሮችን ይፋ አድርጓል፡፡ ፋክሶቹም 24 ሰዓት በመስራት ከአውሮፓና ከተለያዩ የአገሪቱ ክፍሎች ጥቆማዎችን እንደተቀበሉና በአካል ቀርበው ጥቆማቸውን የሚሰጡትንም በተዘጋጀው ቅጽ ላይ ሞልተው በታሸገው የጥቆማ መስጫ ሳጥን ውስጥ እያስገቡ ይገኛሉ” ብለዋል፡፡

በፓትርያርክ ምርጫ ሕገ ደንብ ላይ እጩ የሚሆኑትን አባቶች ከተለዩ በኋላ ከምእመናን የሚቀርቡ ጥያቄዎችና አስተያየቶችን ለመቀበል የ15 ቀናት የጊዜ ገደብ ተቀምጧል፡፡ ነገር ግን አስመራጭ ኮሚቴው የገለጸው በሦስት ቀናት ልዩነት ፓትርያርክ ሆነው የሚመረጡት አባት እንደሚታወቁ ነው፡፡ ይህ አካሔድ ከሕገ ደንቡ ጋር አይጋጭም? የሚለውንም ሲመልሱ “ከምርጫ ሕገ ደንቡ ጋር ተያዞ በቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ ጸድቆ ለአስመራጭ ኮሚቴው የተሰጠ ተጨማሪ ሕግ አለ፡፡ አስመራጭ ኮሚቴውን በሚያስመርጥበት ወቅት ኮሚቴው ሊሰሯቸው የሚገባውን ተግባራት ቋሚ ሲኖዶስ እየተከታተለ አስፈላጊውን ለውጥ ማድረግ እንደሚችል የተገለጸበት ሕግ ነው፡፡ ይህንን ሕግ ተከትሎ የድርጊት መርሐ ግብር አዘጋጅቶ ነው አስመራጭ ኮሚቴው ለቋሚ ሲኖዶስ ያቀረበው፡፡  ቋሚ ሲኖዶስ የቅዱስ ሲኖዶስም ምልዓተ ጉባኤ በሰጠው ሥልጣንና ውክልና መሠረት አስመራጭ ኮሚቴው ያቀረበውን የጊዜ ሰሌዳ ትክክል ነው ብሎ አጽድቆ ሰጥቶታል፡፡ አስመራጭ ኮሚቴው ሕግ የማውጣትም ሆነ ሕግ የመለወጥ ስልጣን የለውም” በማለት የመለሱ ሲሆን ስለቀኑ ማጠር ሲያብራሩም ወደ አብይ ጾም የተቃረበ በመሆኑ ከዚያ በፊት ማጠናቀቅ እንደሚገባ ግንዛቤ ተወስዶ እንደተከናወነ ገልጸዋል፡፡

በመጨረሻም ከ53ቱም አህጉረ ስብከቶች ለመራጭነት ይገኛሉ ተብሎ ይፋ የተደረገው 800 መራጮች ብቻ ናቸው ፡፡ ነገር ግን ሲሰላ ከዚያ በላይ ስለሚሆኑ እንዴት ይታያል? በማለት ለቀረበው ጥያቄም በፓትርያርክ ምርጫው ላይ በመራጭነት የሚሳተፉ ሰዎች 800 ይሆናል የሚለውም እንደ መነሻ የተያዘ እንጂ የመጨረሻ ቁጥር ያለመሆኑን ያብራሩ ሲሆን የአስመራጭ ኮሚቴው አባላትም ከጋዜጠኞች ለቀረቡት ጥያቄዎች ተጨማሪ ምላሽ በመስጠት ተሳትፈዋል፡፡

በጋዜጣዊ መግለጫው ላይ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን አቃቤ መንበረ ፓትርያርክን ጨምሮ 13ቱም አስመራጭ ኮሚቴዎች ተገኝተዋል፡፡

ጥር 30 ቀን 2005 ዓ.ም. አስመራጭ ኮሚቴው በሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ የካቲት 18 ቀን አምስቱ እጩ ፓትርያርኮች ለምእመናን በይፋ እንደሚገለጹ፤ የካቲት 21 ቀን 2005 ዓ.ም ከምሽቱ 12፡00 ሰዓት ላይ የተመረጡት ፓትርያርክ በመገናኛ ብዙሃን እንደሚገለጽና የካቲት 24 ቀን 2005 ዓ.ም. በዓለ ሲመት እንደሚከናወን ማሳወቁ ይታወሳል፡፡

የካቲት 9 ቀን 2005 ዓ.ም.

እንዳለ ደምስሰ


DSC09260

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የ6ኛ ፓትርያርክ አስመራጭ ኮሚቴ የካቲት 8 ቀን 2005 ዓ.ም. በጠቅላይ ቤተ ክህነት በሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ ለፓትርያርክነትእጩ ሆነው የሚቀርቡ ጳጳሳትን ለመምረጥ ካህናትና ምእመናን ጥቆማ እንዲያደርጉ ከየካቲት 1 – 8 ቀን 2005 ዓ.ም. የሰጠው የጊዜ ገደብ መጠናቀቁን አስታወቀ፡፡

 

አስመራጭ ኮሚቴው በአንድ ሳምንት ውስጥ አከናወንኳቸው ያላቸውን ሥራዎች ባቀረበበት በዚሁ መግለጫ በርካታ ምእመናን ለቤተ ክርስቲያኒቱ 6ኛ ፓትርያርክ ሊሆኑ ይገባቸዋል ያሉትን አባት በአካል በመቅረብ እንዲሁም በፋክስ መልእክት በመላክ ጥቆማ መስጠታቸውን ገልጧል፡፡ ከካህናትና ምእመናን የተገኘው ጥቆማም ለአስመራጭ ኮሚቴው በግብአትነት የሚያገለግል ሲሆን ከየካቲት 9 -14 ቀን 2005 ዓ.ም. በወጣው የፓትርያርክ ምርጫ ሕገ ደንብ መሠረት አስመራጭ ኮሚቴው ለይቶ ከሦስት ያላነሱ ከአምስት ያልበለጡ እጩ ፓትርያርኮችን የካቲት 16 ቀን 2005 ዓ.ም. ለቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ እንደሚያቀርብ መግለጫው አመልክቷል፡፡ የምርጫው ሂደት በሰላም ይጠናቀቅ ዘንድም ብፁዐን ሊቃነ ጳጳሳት ፤ ካህናትና ምእመናን እግዚአብሔርን በጸሎት እንዲጠይቁ ኮሚቴው አሳስቧል፡፡  እጩ ሆነው የሚቀርቡ ጳጳሳትን ለመምረጥ ካህናትና ምእመናን ጥቆማ እንዲያደርጉ ከየካቲት 1 – 8 ቀን 2005 ዓ.ም. የሰጠው የጊዜ ገደብ መጠናቀቁን አስታወቀ፡፡

ነቢዩ ዮናስ (ክፍል አንድ) /ለሕፃናት/

የካቲት 8 ቀን 2005 ዓ.ም.

በቤካ ፋንታ /ወልደ ኢየሱስ/

 

ልጆችዬ እንደምን ሰነበታችሁልኝ? እግዚአብሔር ይመስገን አላችሁኝ? ጎበዞች፡፡ ዛሬ ይዤላችሁ የመጣሁት በጣም ደስ የሚል ታሪክ ነው፡፡ ስለዚህ በደንብ ተከታተሉኝ እሺ፡፡

 

በድሮ ጊዜ ነው፣ በጣም በጣም በድሮ ጊዜ አንድ እግዚአብሔርን በጣም የሚወድ ልጅ ነበረ፡፡ ስሙ ዮናስ ይባላል፡፡ ታዲያ ዮናስ ደግ፣ የዋህ፣ ለሰዎች ሁሉ ታዛዥ እና ክፉ ነገርን የማያደርግ ነው፡፡ በዚህ ጥሩ ጸባዩ የተነሣ እግዚአብሔር ዮናስን በጣም ይወደዋል፣ ስሙንም ጠርቶ ያናግረዋል፡፡

መመለስ /ክፍል አንድ/

የካቲት 8 ቀን 2005 ዓ.ም.

ከእንዳለ ደምስሰ

ከቀኑ አሥራ ሁለት ስዓት ፡፡

 

ገነተ ጽጌ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተ ክርስቲያን ስደርስ ልቦናዬን እየተፈታተነኝ ያለውን የዐሳብ ድሪቶ አውልቄ ለመጣል ትንፋሼን ሰብስቤ በረጅሙ ተነፈስኩ፡፡

 

ከተሳለምኩ በኋላ ከዋናው በር በስተግራ በኩል ካለው ዋርካ ሥር አመራሁ፡፡ የሰርክ ስብከተ ወንጌል መርሐ ግብር እየተካሄደ ነው፡፡ አካባቢዬን ቃኘሁ፡፡ ምእመናን አመቺ ነው ባሉት ቦታ ላይ ተቀምጠው የዕለቱን ትምህርት ይከታተላሉ፡፡ መምህሩ በሉቃስ ወንጌል ምዕ.15፥7 -10 ያለውን ኀይለ ቃል ከመጽሐፍ ቅዱስ እያነበቡ ነው፡፡

te 2

ቤተ ክርስቲያን ክርስቲያናዊ መረጃዎችን የመስጠት አቅሟን ማሳደግ እንደሚገባ ተጠቆመ

የካቲት 5 ቀን 2005 ዓ.ም.

በእንዳለ ደምስስ

te 2በማኅበረ ቅዱሳን የጥናትና ምርምር ማእከል አስተባበሪነት “የኢትዮጵያ ቤተ ክርስስቲያን ተልዕኮ በሉላዊቷ ዓለም እና በዘመናዊው ማኅበረሰብ” በሚል ርዕስ ጥናታዊ ጽሑፍ ቀረበ፡፡

 

በማኅበሩ ሕንፃ ውስጥ የካቲት 2 ቀን 2005 ዓ.ም. ጥናታዊ ጽሑፉን ያቀረቡት አቶ ፋንታሁን ዋቄ ሲሆኑ ቀሲስ ዶክተር ደረጀ ሺፈራው መርሐ ግብሩን መርተውታል፡፡ አቶ ፋንታሁን ዋቄ በጥናታቸው ላይ ዘመናዊነትና መዘመን ምንድነው? ዘመናዊነትና መዘመን ለዓለማውያንና ለኦርቶዶክሳዊያን ክርስቲያኖችምን የተለየ ትርጉም ይኖረዋል? የዓለም ተለዋዋጭነት /Dynamizm/ ፍጥነት መገንዘብ፤ ለኦርቶዶክሳዊው ክርስትና ሉላዊነት ምን ይጠቅማል? የቤተ ክርስቲያን መዘመን እንዴት፤ ለምን? በሚሉ ርዕሶች ዙሪያ ሰፊ ትንታኔ ሰጥተዋል፡፡

hege 1

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የፓትርያርክ ምርጫ ሕገ ደንብ

የካቲት 4 ቀን 2005 ዓ.ም.


በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የፖትርያርክ ምርጫ ሕገ ደንብ ዝርዝር እንደሚከተለው እናቀርባለን፡፡

 

asmerach com

ስድስተኛው ፓትርያርክ የሚመረጡበት ጊዜ ይፋ ተደረገ

ጥር 30 ቀን 2005 ዓ.ም.

በዲ/ን ዮሴፍ ይኲኖ አምላ

 

asmerach comስድስተኛውን የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ፓትርያርክ ለማስመረጥ የተቋቋመው አስመራጭ ኮሚቴ ከምርጫው ሂደት ጋርና  በተያያዥ ጉዳዮች ላይ ዛሬ ጥር 30 ቀን 2005 ዓ.ም ለጋዜጠኞች በሰጠው መግለጫ የካቲት 21 ቀን 2005 ዓ.ም ምርጫው ተከናውኖ፣ በዚሁ ዕለት ምሽት 12 ሰዓት ላይ፤ ውጤቱ ለሕዝቡ ይፋ እንደሚደረግ አስታውቋል፡፡

 

“ወበእንተ ዝንቱ አስተርአየ ወልደ እግዚአብሔር ከመ ይሰዐር ግብሮ ለጋኔን”

ጥር 27 ቀን 2005 ዓ.ም.

በዲ/ን ኃይለ ኢየሱስ ቢያ

“የዲያብሎስን  ሥራ ይሽር ዘንድ የእግዚአብሔር ልጅ ተገለጠ፡፡” 1ኛ ዮሐን.3፥8

 

ይህንን ኀይለ ቃል የተናገረው  ቅዱስ ዮሐንስ ወንጌላዊ ነው፡፡ የተናገረበት ምክንያት፡-

የእግዚአብሔር አብ የባሕርይ ልጅ የጌታችን መድኀኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስን መገለጥ /ሰው ሆኖ የማዳን ሥራውን/ መፈጸሙን ለመግለጥ  የተናገረው /የጻፈው ኀይለ ቃል ነው፡፡

  • መገለጥ ማለት ፡- ረቂቁ አምላክ በተአቅቦ ርቀቱን ሣይለቅ ውሱን ሥጋን ውሱኑም ሥጋ በተአቅቦ ውስንነቱን ሳይለቅ ረቂቅ መለኮትን የሆነበት በአጭር ቃል የቃል ግብር ለሥጋ የሥጋ ግብር ለቃል የሆነበት ረቂቅ ምስጢር ነው፡፡ በዚህም ምክንያት ቀዳማዊ ደኃራዊ የሆነው አምላክ ሞት የሚስማማው ሆነ፤ ዘመን የሚቆጠርለት ሥጋ ዘመን የማይቆጠርለት ሆነ፡፡ ሥጋ በማይመረመር ምስጢር የመለኮትን ገንዘብ ገንዘቡ ቢያደርግ “ፊተኛውና መጨረሻው ሕያውም እኔ ነኝ ሞቼም ነበርሁ ከዘላለም እስከ ዘላለም ድረስ ሕያው ነኝ” /ራእ.1፥17/ ማለት የቻለበት ምስጢር ነው፡፡ የረቀቀው ገዝፎ የገዘፈው ረቆ፣ ሰማያዊው ምድራዊ  ምድራዊው ሰማያዊ ሆኖ መታየት ማለት ነው፣  ከዓለም ተሰውሮ የነበረው ምስጢር  ግልጥ ሆኖ መታየት ማለት ነው ይህንንም ምሥጢር ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ በጢሞቴዎስ  መልእክቱ “እግዚአብሔርን የመምሰል ምስጢር ያለጥርጥር ታላቅ ነው፤ በሥጋ የጠገለጠ፣ በመንፈስ የጸደቀ፣ ለመላእክት የታየ፣ በአሕዛብ የተሰበከ፣ በዓለም የታመነ፣ በክብር ያረገ /1ጢሞ 3፥16/ በማለት፡፡ ከልደት እስከ ዓቢይ ጾም መጀመሪያ  ያለው ጊዜ  ዘመነ አስተርእዮ /የመገለጥ ዘመን/ የመታየት ወቅት ይባላል

tinat ena miriemer 05 2005

የጥናት መድረክ

kiduse entonse

እንጦንዮስ አበ መነኰሳት

ጥር  22 ቀን 2005 ዓ.ም.

  • ምንጭ፡- የበረሃው ኮከብ ቅዱስ እንጦንዮስ መጽሐፍ

 

ጨለማ በዋጠው በግብፅ በረሃ ውስጥ ለብዙዎች አርዓያ በሆነ የእምነት ገድል የቅድስናን ብርሃን በማብራቱ የበረሃው ኮከብ ብለው ብዙዎች ይጠሩታል፡፡

 

kiduse entonseብፁዐዊ ቅዱስ እንጦንስ በምንኩስና ሕይወት ለመኖር ከጌታችን ከመድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በተማረው አብነታዊ ትምህርት (ማቴ.4፥1-10) ከዚህ ዓለም ተድላና ደስታ በመራቅ ከሰዎች ሁሉ ተለይቶ  ፍጹም መንፈሳዊ ተጋድሎን በመጋደል በተወለደ በ106 ዓመቱ ጥር 22 ቀን በ356 ዓ.ም. ከዚች ዓለም በሥጋ ተለይቷል፡፡ “ክቡር ሞቱ ለፃድቅ በቅድመ እግዚአብሔር” “የፃድቅ ሰው ሞቱ በእግዚአብሔር ፊት የከበረ ነው” በማለት ክቡር ዳዊት እንደተናገረው፣ “ቅድስት ቤተ ክርስቲያን የቅዱሳን የልደታቸውን ጊዜ፣ የተጋድሏቸውን ሁናቴ፣ ቃል ኪዳን የተቀበሉባቸውንና ያረፉባቸውን ዕለታት በክብር ታስባለች፡፡ ይህም በቅዱስ መጽሐፋችን “የፃድቅ መታሰቢያ ለበረከት ነው”(ምሳ.10÷7)፡፡ በመሆኑም “ስለ ፅድቅ የሚሰደዱ ብጹአን ናቸው ÷ መንግሥተ ሰማያት የእነርሱ ናትና” (ማቴ.5÷8) በሚለው በጌታችን ትምህርት የዚችን ዓለም ጣዕም ንቆ በምናኔ በመኖር ለመነኮሳት አብነት የሚሆናቸውን የቅዱስ እንጦንስን ዜና ሕይወት አቅርበናል፡፡ለመሆኑ ቅዱስ እንጦንስ ማን ነው? አስተዳደጉና የፈጸማቸው አገልግሎቶቹ ምን ይመስላሉ?

“ሰማዕታት የዚችን ዓለም ጣዕም በእውነት ናቁ፤ ደማቸውን ስለ እግዚአብሔር አፈሰሱ፤ ስለ መንግሥተ ሰማያት መራራ ሞትን ታገሱ፡፡”

ጥር 20 ቀን 2005 ዓ.ም.

በዲ/ን ሰሎሞን መኩሪያ

ውዳሴ ማርያም ዘሐሙስ ቁ.6

በረከቱ ይደርብንና ይህንን ቃል የተናገረ የእመቤታችን የቅድስት ድንግል ማርያም ወዳጅ የሆነው ሶሪያዊው ቅዱስ ኤፍሬም ነው፡፡ ቅዱስ ኤፍሬም በብሉይ ዘመን በቅዱስ ዳዊት ሕይወት የተከወነውን በምስጢር ስቦ አምጥቶ የሰማዕታትን ክብር አጎልቶ ተናግሮበታል፡፡ ታሪኩ እንዲህ ነው፡፡ ቅዱስ ዳዊትን እግዚአብሔር አምላክ ለእስራኤል አነገሠው፡፡ በዙሪያው የነበሩ ኤሎፍላዊያንን አጥፍቶ ደብረ ጽዮንን /መናገሻ ከተማውን/ አቅንቶ ሲኖር ከዕለታት አንድ ቀን ዳዊት ታመመ፡፡የዳዊትን መታመም ሰምተው፣ ካሉበት ተነስተው የዳዊትን ከተማ በተለይም ቤተልሔምን ከበቧት፡፡ ዳዊት ይህ ሰምቶ “ወይ እኔ ዳዊት! ድሮ ታመምሁና ጠላቶቼ ሰለጠኑ ሲል የኀያላኑን ልቦና ለመፈተን ከቤተልሔም ምንጭ ውኃ ማን ባመጣልኝ?” አለ፡፡ በዚህ ጊዜ የጭፍሮቹ አለቆች ሦስቱ ማለትም አዲኖን፣ ኢያቡስቴ ኤልያና ረዋታቸውን /የውኃ መያዣ/ ይዘው፣ ጦራቸውን አሰልፈው፣ ጠላቶቹን ድል ነስተው፣ ዳዊት ሊጠጣ የወደደውን ውኃ አመጡለት፡፡ቅዱስ ዳዊትም ያንን ውኃ አፈሰሰው “ለምን አፈሰስከው?” ቢሉት “ደማችሁን መጣጠት አይደለምን?” ብሎ፤ ይህም ከጽድቅ ገብቶ ተቆጠረለት፡፡ 2ሳሙ.23፥13-17

በፌስቡክ የትስስር ገጽ ያግኙን

ስለ ማኅበረ ቅዱሳን መሰረታዊ መረጃዎች

ስያሜ

ማኅበረ ቅዱሳን እግዚአብሔር ያከበራቸው የነቢያት፣ የሐዋርያት፣ የጻድቃንና የሰማዕታት በአጠቃላይ የቅዱሳን ገድል፣ ትሩፋትና አማላጅነት የሚዘከርበት በመሆኑ ‹‹ማኅበረ ቅዱሳን›› የሚል ስያሜውን አግኝቷል፡፡

የማኅበሩ ርእይ

ቤተ ክርስቲያን ሁለንተናዊ የመሪነት ሚናዋን ስትወጣ ማየት

ተልእኮ

ለቤተ ክርስቲያን ተልእኮ መሳካት እና ለሕልውናዋ የሚተጋ፣ የተደራጀ ፣ ምሉዕ ኦርቶዶክሳዊ፤ ርቱዕ ዘመናዊ፤ ሁለገብ መሪ ትውልድ ማፍራት እና ማሰማራት

እሴቶች

  • መንፈሳዊነት

    ኦርቶዶክሳዊነት ርትዕት ሃይማኖት፣ ጽኑ እምነት፣ መልካም ምግባርና መንፈሳዊ እውቀት በአንድነት የተዋሐዱበት፤ አርአያ እግዚአብሔርን አጽንቶ በሐዋርያዊ የሕይወት ተጋድሎ እግዚአብሔርን በግብር ወደ መምሰል የሚታደግበት ፍጹም ሰማያዊ ሕይወት በመሆኑ፤ አባላት በየትኛውም ቦታ፣ ጊዜና ሁኔታ በማሰብ፣ በመናገር እና በመሥራት/በተግባር በሚገለጽ ክርስቲያናዊ ሥነ ምግባር ታንጸው፣ ፍኖተ አበውን ተከትለው፣ በታማኝነት እና በፈሪሐ እግዚአብሔር ቤተ ክርስቲያንን በቅንነት ያገለግላሉ::
  • አገልጋይነት

    የማኅበሩ አባላት አገልግሎትን የክርስቲያናዊ ሕይወታቸው መገለጫ አድርገው በመቀበል በበጎ ፈቃድ ሰማያዊውን ክብርና ጸጋ በመሻት፣ ምድራዊ ክብርና ውዳሴ ከንቱን ሳይፈልጉ፣ በትሕትና እና በክርስቲያናዊ ፍቅር በታማኝነት ያገለግላሉ::
  • የሐሳብ መሪነት

    ማኅበሩ ለቤተ ክርስቲያን ዘላቂ አገልግሎት የሚያስፈልጉ፣ ኦርቶዶክሳዊ እሳቤን የተከተሉና ዘመኑን የዋጁ የመሪነት ሐሳቦችን በማፍለቅ ከሚመለከታቸው የቤተ ክርስቲያን መሪዎች ጋር በመመካከር ይሠራል::
  • ተባባሪነት

    ማኅበሩ የቤተ ክርስቲያን አገልግሎት የሁሉም የቤተ ክርስትያን አካላት የወል ተግባር ነው ብሎ ያምናል:: በመሆኑም እንደየጉዳዩ አግባብነት ካላቸው ባለ ድርሻ እና አጋር አካላት ጋር በመግባባት፣ በመመካከር እና በቅንነት ለተልእኮ አንድነት ብዝኃ ጸጋን በማክበር አብሮ ይሠራል::
  • ሙያ አክባሪነት

    የማኅበሩ አባላት ባላቸው ልዩ ልዩ ሙያ /ዕውቀት/ ቤተ ክርስቲያንን ለማገልገል የተሰባሰቡ በመሆናቸው፣ በማኅበሩ አሠራሮች ሁሉ ከኦርቶዶክሳዊው ትምህርተ ሃይማኖት ጋር በማይጋጩ በእውነተኛ መረጃ ለሚደገፉ ሙያዊ ምክረ ሐሳቦች ተገቢውን ክብርና ቅድሚያ ይሰጣል:: በቤተ ክርስቲያንም ለመንፈሳዊ እና ለዘመናዊው (አስኳላ) ሙያ ተገቢው ክብር እንዲሰጥ ይሠራል::
  • ምክንያታዊ ሞጋችነት

    ማኅበሩ በእውነተኛ መረጃ ላይ ተመሥርቶ ቤተ ክርስቲያንን ከውስጥም ሆነ ከውጭ የሚፈትኑ አስተሳሰቦችን፣ አሠራሮችን፣ ልማዶችን እና ትርክቶችን በግልጽና በመንፈሳዊ ጥብዓት እና በእውነት እንዲሞገቱና መፍትሔ ላይ እንዲደረስ ይሠራል::
  • ተጠያቂነት

    የማኅበሩ አገልግሎት ግብ ሰማያዊ ዋጋ ማግኘት ስለሆነ ኀላፊነትን በአግባቡ አለመወጣት በእግዚአብሔር እና በሰዎች ዘንድ የሚያስጠይቅ በመሆኑ በየትኛውም እርከን ላይ ያለ አባል እና አመራር በማኅበሩ አሠራር መሠረት በተሰጠው ኀላፊነት ተጠያቂ ይሆናል፡፡

ዓላማዎች

  • የቤተ ክርስቲያን ተቋማዊ አስተዳደር፣ የአሠራር ሥርዐትና አስተሳሰብ፣ በቴክኖሎጂ እና በልዩ ልዩ መንገዶች በመደገፍ ዘመኑን ለዋጀ ጠንካራ አገልግሎት ማብቃት፤
  • የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተማሪዎችን ሙሉ ሰብእናን የሚገነባ ሥርዐተ ትምህርት በማስተማር ዘመኑን የዋጁ ምሉዕ ኦርቶዶክሳዊ የሆኑ በቤተ ክርስቲያን አስተዳደራዊ መዋቅር የሚያገለግሉ እንዲሁም በማኅበራዊ፣ በኢኮኖሚያዊ በፖለቲካዊ እና በሀገር አስተዳደር ጉዳዮች መሪ/ንቁ ተሳታፊ አገልጋዮችን ማፍራት እና ማሠማራት፤
  • የተተኪውን ትውልድ ምንጭ ለማጎልበት የሰ/ት/ቤቶችን አቅም በማጠናከር የሕጻናት እና የወጣቶችን የተተኪነት ሚና ማሳደግ፤
  • ኦርቶዶክሳዊ መንፈሳዊነትን በተግባር የሚገልጽ ቤተሰብ እና አንድነቱን የጠበቀ ኦርቶዶክሳዊ ማኅበረሰብ በመገንባት የተደራጀ እና የተናበበ አገልግሎት መስጠት፤
  • በተደራጀ እና ተደራሹን ማእከል ባደረገ መንገድ ስብከተ ወንጌልንና ሐዋርያዊ ተልእኮን ዘርፈ ብዙ በሆኑ መንገዶች በመላው ዓለም ማስፋፋት፤
  • በቤተ ክርስቲያን ላይ የሚነዙትን የርእዮተ ዓለም፣ የሐሰት ትርክቶች እና የአጽራረ ቤተ ክርስቲያንን እንቅስቃሴ ጥናት እና ምርምር ላይ ተመርኩዞ መሞገት እና የተሳሳቱትን በማረም፣ በጠንካራ የዕቅበተ እምነት አገልግሎት የቤተ ክርስቲያንን ሕልውና ማስጠበቅ፤
  • በተመረጡ ገዳማት እና አብነት ትምህርት ቤቶች የልኅቀት ማእከል እና የተለየ ክርስቲያናዊ ተልእኮ የሚፈጽሙ እንዲሆኑ የሚያስችል ሁለገብ የአእምሮ ልማት ድጋፍ ማድረግ፤
  • ማኅበሩ ዘመኑን የዋጀ ተቋማዊ የአሠራር ሥርዓት በመዘርጋት ተልእኮውን ማሳካት የሚችልበት አቅም መፍጥር ( በአመራር፣ በሰው ኃይል፣ በመንፈሳዊነት፣ በግንኙነት፣ በዕውቀት፣በልማት፣ በፋይናንስ፣ በቴክኖሎጂ)፤
  • ዓለም አቀፍ ግንኙነትና የትብብር አገልግሎትን መርሕ ያደረገ የኦርቶዶክሳውያን ኢኮኖሚያዊ፣ ማኅበራዊና ፖለቲካዊ ተሳትፎ ማሳደግ፣

አቡነ ጎርጎርዮስ ካልዕ
የሸዋ ሊቀ ጳጳስ ፲፱፻፴፪-፲፱፻፹፪ዓ.ም.

የማኅበሩ ህንጻ