መንፈሳዊነት
ኦርቶዶክሳዊነት ርትዕት ሃይማኖት፣ ጽኑ እምነት፣ መልካም ምግባርና መንፈሳዊ እውቀት በአንድነት የተዋሐዱበት፤ አርአያ እግዚአብሔርን አጽንቶ በሐዋርያዊ የሕይወት ተጋድሎ እግዚአብሔርን በግብር ወደ መምሰል የሚታደግበት ፍጹም ሰማያዊ ሕይወት በመሆኑ፤ አባላት በየትኛውም ቦታ፣ ጊዜና ሁኔታ በማሰብ፣ በመናገር እና በመሥራት/በተግባር በሚገለጽ ክርስቲያናዊ ሥነ ምግባር ታንጸው፣ ፍኖተ አበውን ተከትለው፣ በታማኝነት እና በፈሪሐ እግዚአብሔር ቤተ ክርስቲያንን በቅንነት ያገለግላሉ::
ወቅታዊውን ጉዳይ አስመልክቶ ቅዱስ ሲኖዶስ መግለጫ አወጣ
ጥር 9 ቀን 2005 ዓ.ም.
በዲ/ን ዮሴፍ ይኩኖአምላክ
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ ወቅታዊውን ጉዳይ በማስመልከት፤ ትናንት ረቡዕ ጥር 8 ቀን 2005 ዓ.ም ባወጣው ባለ 5 ገጽ መግለጫ፥ በ3 ዐበይት ጉዳዮች ላይ ውይይት አድርጎ ውሳኔ አሳልፏል፡፡
ቅዱስ ሲኖዶስ የመከረባቸውን አጀንዳዎችና ያተላለፈውን ውሳኔ የያዘው የመግለጫውን ሙሉ ቃል አቅርበነዋል፡፡
ከተራ ምንድን ነው?
ጥር 9 ቀን 2005 ዓ.ም.
መ/ር ሳሙኤል ተስፋዬ
ጥያቄ
በየዓመቱ የጥምቀት በዓል በድመቀት ይከበራል፡፡ ከበዓሉ በፊት የከተራ በዓል የሚከበርበትን ታሪካዊና ሃይማኖታዊ ፋይዳውን ብታብራሩልን
ዮስቲና ከአዲስ አበባ
መልሱ
ከተራ ከበበ ካለው የግእዝ ግሥ የወጣ ነው፡፡ ፍችው ውኃ መከተር፣ መገደብ ማለት ነው፡፡ የጥምቀት ዋዜማ ታቦተ ሕጉ ከቤተ መቅደስ ወጥቶ ውኃ ባለበት አካባቢ ስለሚያድር የየአጥቢያው ሕዝብ እየተሰበሰበ በወንዝ ዳር ወይም በምንጭ አካባቢ ድንኳን ይተከላል፡፡ ድንኳንም ከሌለ ዳስ ሲጥል ይውላል፡፡ የምንጮች ውኃ ደካማ በመሆኑ እንዲጠራቀም ይከተራል ጉድጓድ እየተቆፈረ ውኃው እንዳይሄድ ይገደባል፡፡
የደብረ ምጥማቅ ጻድቃኔ ቅድስት ማርያም ቤተ ክርስቲያን ሕንፃ ግንባታ በመፋጠን ላይ መሆኑ ተገለጸ
ጥር 8 ቀን 2005 ዓ.ም.
በእንዳለ ደምስስ
ደብረ ምጥማቅ የጻድቃኔ ቅድስት ማርያም ቤተ ክርስቲያንን በዘመናዊ መልክ ለመገንባት እንዲቻል አዲስ አበባ ቦሌ አካባቢ በሚገኘው ደሳለኝ ሆቴል ታኅሣሥ 21 ቀን 2005 ዓ.ም. ከምሽቱ 12፡00 ሰዓት ጀምሮ የገቢ ማሰባበሰቢያና የምክክር መርሐ ግብር የተዘጋጀ ሲሆን በመርሐ ግብሩ ላይ ብፁዕ አቡነ ሰላማ የማእከላዊ ትግራይ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ተገኝተዋል፡፡ ብፁዕነታቸው መርሐ ግብሩን በጸሎት ከከፈቱ በኋላ በሰጡት ቃለ ምዕዳን “የዚህ ታላቅና ታሪካዊ ቤተ ክርስቲያን ግንባታ ላይ መሣተፍ ባለ ታሪክ ከማድረጉም ባሻገር የቀደሙ ነገሥታትን አርዓያ መከተል ነው፡፡ በዚህም መሠረት ቤተ ክርስቲያኑን ተባብረን እንድንሠራውና የታሪኩ ተካፋይ እንድንሆን ከእኛ ይጠበቃል” ብለዋል፡፡
ብፁዓን ገባርያነ ሰላም
ጥር 3 ቀን 2005 ዓ.ም.
በፍጡርና በፈጣሪ፤ በፍጡርና በፍጡር መካከል ችግሮችና አለመግባባቶች መፈጠራቸው የዚህ ዓለም ባሕርያዊ ግብር ነው፡፡ በተለይም የሰው ልጅ አለመግባባቶችን ዕለታዊ ባሕርዩ ወደ ማድረግ የደረሰም ይመስላል፡፡ ቅዱሳት መጻሕፍትም የእነዚህን ችግሮች ክሡትነት መጠቆማቸውም የሚሰወር አይደለም፡፡
አስቀድመን እንደገለጽነው ሰው በሰብአዊነቱ ከራሱ ጋር፣ ከፈጣሪው ጋርና ከሌሎቹም ሥነ ፍጥረታት ጋር የሚያጋጩት ብዙ ምክንያቶች አሉ፡፡ ከዚህም የተነሣ “ለምን ግጭት ተከሠተ” ብሎ መሞገት ጊዜ መጨረስ ሲሆን “ለምን አልታረቅሁም” ብሎ ራስን መጠየቅ ግን አግባብ ነው፡፡ ምክንያቱም የዕርቀ ሰላም መንገዶች እንደ ግጭቱ መንገድ የተንዛዙ ሳይሆኑ የተቆጠሩና የተሰፈሩ የተለኩ ሃይማኖታዊ እሴቶች ናቸውና፡፡
የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዐተ ጉባኤ ለዕርቀ ሰላሙ ቅድሚያ ሰጥቶ እንደሚመክር ታወቀ
ጥር 3 ቀን 2005 ዓ.ም.
ጥበብ ዘየዓቢ እምነ ኩሉ ጥበብ ከጥበብ ሁሉ የሚበልጥ ጥበብ
ጥር 1 ቀን 2005 ዓ.ም.
ከሰማይ በታች ባሉት ፍጥረታት ላይ በገዢነት የተሾመው የዕለተ ዓርብ ፍጥረት የሰው ልጅ በምክረ ከይሲ ተታልሎ ከፈቃደ እግዚአብሔር ፈቀቅ በማለቱ ሞትን ወደ ዓለም አስገብቷል፡፡ በዚህም የተሰጠውን ነጻነት በገዛ ፈቃዱ አሳልፎ ሰጠ በምትኩም ወደ ሰይጣን ምርኮኝነት እና ጽኑ አገዛዙ ፈጽሞ ሄደ፡፡
እነሆ ዛሬ በዳዊት ከተማ መድኀኒት ተወልዶላችኋል ሉቃ.2፥11
ታኅሣሥ 27 ቀን 2005 ዓ.ም.
መጋቤ ብሉይ አእምሮ ዘውዴ
እንኳን ለጌታችን ለመድኀኒታችን ለኢየሱስ ክርስቶስ የልደት በዓል በሰላም አደረሳችሁ፡፡
የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስ ልደት እንደ እንግዳ ደራሽ እንደ ውኃ ፈሳሽ አይደለም፡፡ ከጥንት ከመሠረት ጀምሮ በመላእክት፤ በነቢያት ሲነገር፤ ሲሰበክ የመጣ ነው እንጂ፡፡ ማቴ.1፥18፡፡
ሰው የመሆኑን ምሥጢር ለመጀመሪያ ጊዜ በማእከለ ገነት የተናገረ እርሱ እግዚአብሔር ነው፡፡
ብፁዕ አቡነ ናትናኤል የእንኳን አደረሳችሁ መልእክት አስተላለፉ፡፡
ታኅሣሥ 26 ቀን 2005 ዓ.ም.
በዲ/ን ዮሴፍ ይኲኖ አምላክ
የሕፃኑ የኢየሱስ ልደት /ለሕፃናት/
ታኅሣሥ 26 ቀን 2005 ዓ.ም.
ከወልደ ኢየሱስ /ቤካ ፋንታ/
ልጆችዬ እንደምን ሰነበታችሁ? ዛሬ ስለ ታላቁ ሕፃን ልደት የምነግራችሁ ነገር አለና በማስተዋል ተከታተሉኝ እሺ፡፡ ጎበዞች!
የዛሬ ሁለት ሺ ዓመት ገደማ ነው፡፡ በኢየሩሳሌም ሀገር ንጉሡ ሄሮድስ ሕዝቡን ሁሉ ቤተልሄም ወደምትባል ከተማ ጠራቸው፡፡ እመቤታችንም በዚያ ጊዜ የአሥራ አምስት/15/ ዓመት ልጅ ሆኖ በሚጠብቃት በአረጋዊው /በሽማግሌው/ ዮሴፍ ቤት ትኖር ነበር፡፡ እመቤታችን ድንግል ማርያም ሕፃኑን ኢየሱስ ክርስቶስን ፀንሳ ልትወልድ ደርሳ ሳለ ወደ ቤተልሄም ከተማ ከአረጋዊው ጠባቂዋ ዮሴፍና ከቅድስት ሰሎሜ ጋር ሄደች፡፡
“ወብዙኀን ይትፌሥሑ በልደቱ በመወለዱም ብዙዎች ደስ ይላቸዋል” ሉቃ.1፥14
ታኅሣሥ 25 ቀን 2005 ዓ.ም.
ዲ/ን ዮሴፍ ይኲኖ አምላክ