መንፈሳዊነት
ኦርቶዶክሳዊነት ርትዕት ሃይማኖት፣ ጽኑ እምነት፣ መልካም ምግባርና መንፈሳዊ እውቀት በአንድነት የተዋሐዱበት፤ አርአያ እግዚአብሔርን አጽንቶ በሐዋርያዊ የሕይወት ተጋድሎ እግዚአብሔርን በግብር ወደ መምሰል የሚታደግበት ፍጹም ሰማያዊ ሕይወት በመሆኑ፤ አባላት በየትኛውም ቦታ፣ ጊዜና ሁኔታ በማሰብ፣ በመናገር እና በመሥራት/በተግባር በሚገለጽ ክርስቲያናዊ ሥነ ምግባር ታንጸው፣ ፍኖተ አበውን ተከትለው፣ በታማኝነት እና በፈሪሐ እግዚአብሔር ቤተ ክርስቲያንን በቅንነት ያገለግላሉ::




የኢየሩሳሌም መታሰቢያ ድርጅት የተመሠረተበትን 50ኛ ዓመት አከበረ
ግንቦት 19 ቀን 2006 ዓ.ም.
በእንዳለ ደምስስ
አሰግድመኝ ቅድስት ማርያም ክፍል ሁለት
ግንቦት 19 ቀን 2006 ዓ.ም.
በእንዳለ ደምስስ
በካህናቱ መሪነት ከተራራው ሥር ወደምትገኘው ወደ ቀድሞ ዋሻ ቤተ ክርስቲያን ስናመራ፤ ከተራራው አናት ላይ ሆነን ቁልቁል ስንመለከት ትልቅ ወንዝና ደረቱን ለኛ የሰጠ ተራራ ተመለከትን ፡፡ ካህናቱንና ዲያቆናቱን ተከትለን ቁልቁል የሚወስደውን
ቀጭን መንገድ ተያያዝነው፡፡ ወንዙ ምን ይባላል አልናቸው ለአንድ አዛውንት “ የማርያም ዥረት ነው የሚባለው” አሉን ፡፡ እንደመቀነት የሚጠማዘዘውን ቀጭን መንገድ እየተከተልን ወደ ዋሻው አፋፍ ደረስን፡፡ ወደ ዋሻው መግቢያ በስተቀኝ በኩል በመጠኑ የጎደጎደ ሥፍራ ይታያል፡፡ ምን እንደሆነ ጠየቅን፡፡ “ከተራራው ሥር እየፈለቀ የሚወርድ ማየገቦ የሚጠራቀምበት ጉድጓድ ነበር፤ (ማየገቦ አምላካችን ኢየሱስ ክርስቶስ በተሰቀለ ጊዜ በቦታው ያልነበረው አንድ ዓይና ሌንጊኖስ ከአይሁድ ጋር ለመተባበር ብሎ ኢየሱስ ክርስቶስን በጦር ቢወጋው ውኃና ደም እንደ ለ ፊደል ፈሷል ፡፡ የፈሰሰው ውኃ ማየገቦ ይባላል፡፡) ዋሻው ቤተ መቅደስ ከተደረመሰ በኋላ ደርቋል” አሉን አዛውንቱ፡፡
ሐዊረ ሕይወት በሀገረ ጀርመን ተካሄደ
ግንቦት 15 ቀን 2006 ዓ.ም.
ከጀርመን ቀጣና ማእከል
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ማኅበረቅዱሳን አውሮፓ ማእከል የጀርመን ቀጣና ማእከል በአውሮፓ የመጀመሪያውን የሐዊረ ሕይወት መርሐ ግብር ከግንቦት 8-10, 2006 በክሩፈልባክህ (Kroeffelbach) በሚገኘው የኮፕቲክ
ቅዱስ እንጦንስ ገዳም (Sankt-Antonius Kloster) በደማቅ ሁኔታ አካሄደ።
በዚህ ከ80 በላይ ምእመናን በተሳተፉበት መርሐ ግብር ላይ ሰፊ ትምህርት የተሰጠ ሲሆን በተለይ ነገረ ድኅነት እና መንፈሳዊ አገልግሎት ላይ የተሰጡት ጥልቅ ትምህርቶች ተሳታፊዎች በጉዳዮቹ ላይ የነበራቸውን እውቀት በከፍተኛ ሁኔታ ያሳደጉ እና ታዳሚው ሐዊረ ሕይወት በቅርቡ ይደገምልን የሚል ጥያቄን እንዲሰነዝር ያነሳሱ ነበሩ። በተጨማሪም መዝሙራት በዘማርያንና በሕብረት የቀረቡ ሲሆን ማኅበረ ቅዱሳን በሀገር ቤት ስብከተ ወንጌልን ለማስፋፋትበተለይም በተመረጡ ጠረፍና ገጠር አብያተ ክርስቲያናት ላይ አቅዶ እያከናወነው ስላለው የስብከት ወንጌል ማስፋፊያ ፕሮግራም ገለጻ ተደርጓል።
ሐዊረ ሕይወት(አዳማ ማዕከል)
“የእግዚአብሔር መንፈስ ያለበት መጽሐፍ ሁሉ ለትምህርትና ለተግሣጽ. . . ይጠቅማል” 2ኛ ጢሞ.3፤16-17
ግንቦት 12 ቀን 2006 ዓ.ም.
በዲ/ን ዮሴፍ ይኲኖአምላክ
አሰግድመኝ ቅድስት ማርያም ገዳም
ግንቦት 11 ቀን 2006 ዓ.ም.
በእንዳለ ደምስስ
የቅዱስ ሲኖዶስ ምልኣተ ጉባኤ የ2006 ዓ.ም. ሁለተኛ መደበኛ ጉባኤ ተጀመረ
ግንቦት 6 ቀን 2006 ዓ.ም.
በእንዳለ ደምስስ
ለአብነት መምህራንንና ተማሪዎች የሕክምና አገልግሎት ተሰጠ
ሚያዚያ 30 ቀን 2006 ዓ.ም.
በዲ/ን ቴዎድሮስ ኃይሉ
በጠረፋማ አካባቢዎች ለተጠመቁ ወገኖች አብያተ ክርስቲያናት ለማነጽ ጥረት እየተደረገ ነው
ሚያዚያ 30 ቀን 2006 ዓ.ም.
በእንዳለ ደምስስ
በጂንካ፤በግልገል በለስ፤ በቦረና /ተልተሌ/፤ በቦንጋ/ጮራ/ እንዲሁም በሌሎች ጠረፋማ ወረዳዎች ነዋሪዎች ጥምቀት ተከናውኖላቸው የነበረ ቢሆንም ቤተ ክርስቲያን ሳይሠራላቸው ቆይቷል፡፡ የስብከተ ወንጌል ማስፋፊያ ፕሮግራምም ይህንን ችግር ለመፍታት ቤተ ክርስቲያን ለመሥራት ከፍተኛ ጥረት እያደረገ ይገኛል፡፡ ቤተ ክርስቲያን በማጣት ከአገልግሎት ርቀው ወደ ኢ-አማኒነት እንዳይመለሱ ምእመናን እገዛ ማድረግ እንደሚገባቸው የጠቀሰው የስብከተ ወንጌል ማስፋፊያው በቅርቡ ሊሠሩ ለታቀዱ ለ12 አብያተ ክርስሰቲያናት የግንባታ ግብአቶችን፤ በተለይም ቆርቆሮ፤ ምስማር፤ እንዲሁም ሌሎች ቁሳቁሶችን ምእመናን እንዲረዱ የቁሳቁስ ድጋፍ ማድረጊያ መርሐ ግብር በማኅበሩ ጽ/ቤት አዘጋጅቷል፡፡
“ሞቱንም በሚመስል ሞት ከእርሱ ጋር ከተባበርን ትንሣኤውን በሚመስል ትንሣኤ ደግሞ ከእርሱ ጋር እንተባበራለን፡፡” ሮሜ 6፡5
ሚያዚያ 30 ቀን 2006 ዓ.ም.
በመ/ር ሳሙኤል ተስፋዬ
በጥንተ ጠላት ዲያቢሎስ አሳሳችነት አዳምና ሔዋን የእግዚአብሔርን ሕግ በመተላላፋቸው ሞተ ሥጋና ሞተ ነፍስ ተፈርዶባቸው ነበር፡፡ የዓለም መድኃኒት ኢየሱስ ክርስቶስ አዳምና ሔዋን ከክህደት የደረሱት በዲያቢሎስ አሳሳችነት በመሆኑና ለሰው ልጆች ካለው ፍጹም ፍቅር የተነሳ የተፈረደባቸውን ሞት በሞቱ ሊደመስስ ሰው ሆነ፡፡ ዮሐ1፡1 ከእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ተወለደ፡፡ 30 ዓመት ሲሞላው ተጠመቀ፡፡ እንደተጠመቀም ልዋል ልደር ሳይል ገዳመ ቆሮንቶስ ሄደ፡፡ በዚያም ጾመ ጸለየ በዲያቢሎስም ተፈተነ፡፡ ሦስት ዓመት ከሦስት ወር ካስተማረ በኋላ አስቀድሞ ለአዳምና ለሔዋን ሞታቸውን ሊደመስስ፡፡ ዕዳቸውን ደመስሶ ነጻ ሊያደርጋቸው በገባው ቃል ኪዳን መሠረት መከራ ተቀበለ፤ በአይሁድ ሸንጎ ፊት ቆመ፣ ምራቅ ተተፋበት፣ ተገረፈ፣ በገመድ ታስሮ ተጎተተ፣ በመስቀል ተሰቅሎ ሞተ የአዳምና የሔዋንን ዕዳ በደል ደመሰሰ፡፡ ሞት ድል ተነሳ፡፡ ማቴ. 27-28