መንፈሳዊነት
ኦርቶዶክሳዊነት ርትዕት ሃይማኖት፣ ጽኑ እምነት፣ መልካም ምግባርና መንፈሳዊ እውቀት በአንድነት የተዋሐዱበት፤ አርአያ እግዚአብሔርን አጽንቶ በሐዋርያዊ የሕይወት ተጋድሎ እግዚአብሔርን በግብር ወደ መምሰል የሚታደግበት ፍጹም ሰማያዊ ሕይወት በመሆኑ፤ አባላት በየትኛውም ቦታ፣ ጊዜና ሁኔታ በማሰብ፣ በመናገር እና በመሥራት/በተግባር በሚገለጽ ክርስቲያናዊ ሥነ ምግባር ታንጸው፣ ፍኖተ አበውን ተከትለው፣ በታማኝነት እና በፈሪሐ እግዚአብሔር ቤተ ክርስቲያንን በቅንነት ያገለግላሉ::




ማኅበረ ቅዱሳን በኦሮምኛ ቋንቋ የድረ – ገጽ አገልግሎት ሊጀምር ነው
ሰኔ 13 ቀን 2006 ዓ.ም
በእንዳለ ደምስስ
በማኅበረ ቅዱሳን የኅትመትና ኤሌክትሮኒክስ ሚዲያ ዋና ክፍል የኦሮምኛ ድረ ገጽ አገልግሎት በቅርቡ እንደሚጀምር የዋና ክፍሉ ሓላፊ ዲያቆን ዶ/ር መርሻ አለኸኝ ገለጹ፡፡
ቅድስት አፎሚያ
ሰኔ 12 ቀን 2006 ዓ.ም.
በመ/ር ፍቃዱ ሣህሌ
በወርኃ ሠኔ መታሰቢያ ከሚደረግላቸው ቅዱሳን መካከል እግዚአብሔርን የሚፈራ የአስተራኒቆስ ሚስት የሆነች የቅድስት አፎምያን ታሪክ በአጭሩ እንዳስሳለን፡፡
ቅድስት አፎምያ በትዳር በነበረችባቸው ዘመናት እግዚአብሔርን ከሚወድ ባለቤቷ ጋር እግዚአብሔርን ስታገለግለው የኖረች ሴት ነበረች፡፡ በየወሩ በ29 ቀን የጌታችንን የልደቱን፣ ወር በገባ በ21 የእመቤታችንንና ወር በገባ በ12 የቅዱስ ሚካኤልን መታሰቢያ እያደረጉ ነዳያንን ይጎበኙ እንደነበር ታሪካቸው ይነግረናል፡፡
ለማእከላት ሓላፊዎች የአቅም ማጎልበቻ ሥልጠና ተሰጠ
ሰኔ 12 ቀን 2006 ዓ.ም.
በሕዝብ ግንኙነት አገልግሎት
ማኅበረ ቅዱሳን ለማእከላት፤ ለማስተባበሪያ ጽ/ቤት ሓላፊዎችና አስተባባሪዎች ከሰኔ 10- 11 ቀን 2006 ዓ.ም. ሁለት ቀናት የቆየ የአቅም ማጎልበቻ ሥልጠና ሰጠ፡፡
በሥልጠናው ከሀገር ውስጥና ከውጪ የተውጣጡ የ25 ማእከላት ጸሐፊዎች፤ የማስተባበሪያ ጽ/ቤት ሓላፊዎች፤ የግቢ ጉባኤያት አስተባባሪዎችና መምህራን መካፈላቸውን የማኅበረ ቅዱሳን የሰው ሀብት ሥራ አመራርና ጠቅላላ አገልግሎት ክፍል ሓላፊ አቶ ዳንኤል ተስፋዬ ገልጸዋል፡፡
ለማእከላት ሓላፊዎች የአቅም ማጎልበቻ ሥልጠና ተሰጠ
ሰኔ 12 ቀን 2006 ዓ.ም.
በሕዝብ ግንኙነት አገልግሎት
ማኅበረ ቅዱሳን ለማእከላት፤ ለማስተባበሪያ ጽ/ቤት ሓላፊዎችና አስተባባሪዎች ከሰኔ 10- 11 ቀን 2006 ዓ.ም. ሁለት ቀናት የቆየ የአቅም ማጎልበቻ ሥልጠና ሰጠ፡፡
በሥልጠናው ከሀገር ውስጥና ከውጪ የተውጣጡ የ25 ማእከላት ጸሐፊዎች፤ የማስተባበሪያ ጽ/ቤት ሓላፊዎች፤ የግቢ ጉባኤያት አስተባባሪዎችና መምህራን መካፈላቸውን የማኅበረ ቅዱሳን የሰው ሀብት ሥራ አመራርና ጠቅላላ አገልግሎት ክፍል ሓላፊ አቶ ዳንኤል ተስፋዬ ገልጸዋል፡፡
ጉባኤ ቃና
የደብረ ሊባኖስ ገዳምን ለመታደግ ጥሪ ቀረበ
ሰኔ 10 ቀን 2006 ዓ.ም.
በእንዳለ ደምስስ
የደብረ ሊባኖስ ገዳም የልማት ፕሮጀክት ትግበራ በመፋጠን ላይ ይገኛል
ሰኔ 5 ቀን 2006 ዓ.ም.
በእንዳለ ደምስስ
የጥናት ቡድኑ በገዳሙ የሚታዩትን ዋና ዋና ችግሮች በመለየትና ጥናት በማካሔድ፤ የፕሮጀክት ሰነድ በማዘጋጀት ወደ ተግባር ለመሸጋገር በርካታ ሥራዎችን ሲሠራ ቆይቷል፡፡
ብፁዕ አቡነ አብርሃም አዲሱን መንበረ ጵጵስና ተረከቡ
ሰኔ 3 ቀን 2006 ዓ.ም.
ሊ/ዲ/ ኤፍሬም የኔሰው
የሀገር አቀፍ የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት ጠቅላላ ጉባኤ ተጠናቀቀ
ሰኔ 2 ቀን 2006 ዓ.ም.
የማቴዎስ ወንጌል
ሰኔ 2 ቀን 2006 ዓ.ም
ካለፈው የቀጠለ
ይሁዳ የእግዚአብሔር አብ
ኤራስ ዓዶሎማዊ የቅዱስ ገብርኤል
በግ የእግዚአብሔር ወልድ
ቀለበት፡- የሃይማኖት፤ ባርኔጣ፡- የአክሊለ ሦክ፤ በትር የመስቀል ትዕማር የቤተ አይሁድ፡፡ ትዕማር መያዣ ይዛ ቀረች እንጂ ዋጋዋን እንዳላገኘች ቤተ አይሁድም ትንቢቱን ተስፋውን ሰምተው ቀሩ እንጂ በክርስቶስ አላመኑምና፡፡
ፋሬስ የኦሪት ዛራ የወንጌል ምሳሌ፡፡ ዛራ አስቀድሞ እጁን እንዳወጣ፡፡ ወንጌልም በመልከ ጼዴቅ ታይታ ጠፍታለችና፡፡ ፋሬስ እሱን ወደኋላ ስቦ እንደተወለደ በመካከል ኦሪት ተሠርታለች፡፡ ዛራ በኋላ እንደተወለደ ወንጌል ኋላ ተመሥርታለችና፡፡