መንፈሳዊነት
ኦርቶዶክሳዊነት ርትዕት ሃይማኖት፣ ጽኑ እምነት፣ መልካም ምግባርና መንፈሳዊ እውቀት በአንድነት የተዋሐዱበት፤ አርአያ እግዚአብሔርን አጽንቶ በሐዋርያዊ የሕይወት ተጋድሎ እግዚአብሔርን በግብር ወደ መምሰል የሚታደግበት ፍጹም ሰማያዊ ሕይወት በመሆኑ፤ አባላት በየትኛውም ቦታ፣ ጊዜና ሁኔታ በማሰብ፣ በመናገር እና በመሥራት/በተግባር በሚገለጽ ክርስቲያናዊ ሥነ ምግባር ታንጸው፣ ፍኖተ አበውን ተከትለው፣ በታማኝነት እና በፈሪሐ እግዚአብሔር ቤተ ክርስቲያንን በቅንነት ያገለግላሉ::
ቅዱስ ታዴዎስ ሐዋርያ
ሐምሌ ፩ ቀን ፳፻፰ ዓ.ም
በዝግጅት ክፍሉ
ሐምሌ ፪ ቀን ከ፲፪ቱ ሐዋርያት አንዱ የኾው የቅዱስ ታዴዎስ የዕረፍቱ መታሰቢያ በዓል ነው፡፡ ከመጽሐፈ ስንክሳርና ከገድለ ሐዋርያት ያገኘነውን የሐዋርያው ታዴዎስን ታሪክ በአጭሩ እነሆ፤
ሊቀ ማእምራን ወመጋቤ ሐዲስ ወልደ ሰንበት ባይነሳኝ ዐረፉ
ሐምሌ ፩ ቀን ፳፻፰ ዓ.ም
በዲያቆን ቴዎድሮስ ኃይሉ
በሕይወት ዘመናቸው ኹሉ ደከመኝ ሰለቸኝ ሳይሉ ቅድስት ቤተ ክርስቲያንን በቅንነትና በታማኝነት ሲያገለግሉ የነበሩት ታላቁ የቤተ ክርስቲያን ሊቅ፣ የትሕትናና የጸሎት አባት ሊቀ ማእምራን ወመጋቤ ሐዲስ ወልደ ሰንበት ባይነሳኝ ዐረፉ፡፡
የካናዳ ማእከል ፲፪ኛ ጠቅላላ ጉባኤ ተካሔደ
ሐምሌ ፩ ቀን ፳፻፰ ዓ.ም
በካናዳ ማእከል
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን በሰንበት ት/ቤቶች ማደራጃ መምሪያ ማኅበረ ቅዱሳን የካናዳ ማእከል ፲፪ኛ ጠቅላላ ጉባኤ ከሰኔ ፳፭-፳፯ ቀን ፳፻፰ ዓ.ም በሀገረ ካናዳ አልበርታ ግዛት በካልጋሪ ከተማ ተካሔደ፡፡
የሕንፃ ቤተ ክርስቲያኑ ቃጠሎ መንሥኤ እየተጣራ ነው
ሐምሌ ፩ ቀን ፳፻፰ ዓ.ም
በዲያቆን ተመስገን ዘገየ
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን በደቡብ ጎንደር ሀገረ ስብከት በስማዳ ወረዳ ቤተ ክህነት ሽሜ አዝማቾ ቀበሌ በምትገኘው በሽሜ ማርያም ሕንፃ ቤተ ክርስቲያን ላይ የደረሰው የእሳት ቃጠሎ መንሥኤ በወረዳው ፖሊስ ጽ/ቤት እየተጣራ እንደሚገኝ የወረዳ ቤተ ክህነቱ ሊቀ ካህን ቄስ ሞላ ጌጡ ተናገሩ፡፡
ቅዱስ ዮሐንስ መጥምቀ መለኮት
ሰኔ ፴ ቀን ፳፻፰ ዓ.ም
በዝግጅት ክፍሉ
እንደሚታወቀው ሰኔ ፴ ቀን ቅዱስ ዮሐንስ መጥምቀ መለኮት የተወለደበት ዕለት ነው፡፡ በዛሬው ዝግጅታችን የመጥምቁ ዮሐንስን ታሪክ በአጭሩ እናቀርብላችኋለን፤
*ከቃል በላይ ትኩረት ለቅዱስ ያሬድ*
ሰኔ ፳፰ ቀን ፳፻፰ ዓ.ም
በዲያቆን ኤፍሬም የኔሰው
እሑድ ሰኔ ፳፮ ቀን ፳፻፰ ዓ.ም በጠቅላይ ቤተ ክህነት አዳራሽ አንድ ልዩ መርሐ ግብር ተካሒዷል፡፡ መርሐ ግብሩን ያዘጋጀው የማኅበረ ቅዱሳን ትምህርትና ሐዋርያዊ አገልግሎት ዋና ክፍል ሲኾን፣ ዓላማውም የቤተ ክርስቲያናችን ብርሃን፣ የአገራችን ጌጥ የኾነውን ቅዱስ ያሬድንና ሥራዎቹን መዘከር ነው፡፡
የቤተ ክርስቲያን ትምህርት የመልካም ምግባር መሠረት!
ሰኔ ፳፯ ቀን ፳፻፰ ዓ.ም
በዲያቆን ኤፍሬም የኔሰው
የማኅበረ ቅዱሳን ጥናትና ምርምር ማእከል ሰኔ ፳፬ ቀን ፳፻፰ ዓ.ም በማኅበሩ ሕንፃ ሦስተኛ ፎቅ አዳራሽ የጥናት ጉባኤ አዘጋጅቶ ነበር፡፡
ምሩቃኑ ስለ መልካም አስተዳደር እንዲያስተምሩ ፓትርያርኩ መመሪያ ሰጡ፡፡
ሰኔ ፳፯ ቀን ፳፻፰ ዓ.ም
በዲያቆን ኤፍሬም የኔሰው
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ሦስቱም መንፈሳውያን ኮሌጆች የዘር ወቅት በኾነው በወርኃ ሰኔ ደቀ መዛሙርታቸውን አስመርቀዋል፡፡
በአተ ክረምት
ሰኔ ፳፭ ቀን ፳፻፰ ዓ.ም
በዲያቆን ኤፍሬም የኔሰው
የተወደዳችሁ የድረ ገጻችን ተከታታዮች! በዛሬው ዝግጅታችን ስለ ዘመነ ክረምት መግባት፣ ሰኔ ፳፮ ቀን (በዕለተ ሰንበት) ስለሚነበቡ ምንባባትና ስለሚዘመረው መዝሙር የሚያስረዳ አጭር ጽሑፍ እንደሚከተለው ይዘንላችሁ ቀርበናል፤
ዐውደ ርእዩ በሺሕ በሚቈጠሩ ምእመናን እየተጐበኘ ነው፡፡
ሰኔ ፳፭ ቀን ፳፻፰ ዓ.ም
በዲያቆን ኤፍሬም የኔሰው
የኦርቶዶክሳዊት ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያንን አስተምህሮዋን እንጠንቅቅ፤ ድርሻችንን እንወቅ በሚል መሪ ቃል የአዳማ ማእከል በምሥራቅ ሸዋ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ በብፁዕ አቡነ ጎርጎርዮስ መልካም ፈቃድ በአዳማ ከተማ በደብረ ናዝሬት ኢየሱስ ደብር ያዘጋጀው ዐውደ ርእይ ከሰኔ ፲፯ ቀን ፳፻፰ ዓ.ም ጀምሮ በሺሕ በሚቈጠሩ የናዝሬት (የአዳማ) ከተማና የአካባቢው ምእመናን እየተጐበኘ ይገኛል፡፡