‹‹ወወፅኡ እምዐውድ እንዘ ይትፌሥሑ፤ ከሸንጐው ፊት ደስ እያላቸው ወጡ››(የሐዋ. ሥራ ፭፥፵፩)
……እንግድህ ወደተነሣንበት ርእሳችን ስንመጣ ቅዱሳን ሐዋርያቱ በክርስቶስ ስም ከሚደርስባቸው መከራ ይልቅ ስለ ስሙ በሚቀበሉት መከራ የሚያገኙት ጸጋ እጅግ የሚበዛ መሆኑን በመረዳ ነውና ሁልጊዜም ከከሳሾቻቸው ፊት ደስ እያላቸው ይወጡ ነበር፡፡ በዚህ መከራቸውም በሞቱ መስለውታል የትንሣኤውም ተካፋዮች ሆነዋል፡፡