“ለሁለንተናዊ የቤተ ክርስቲያን እድገት የድርሻችንን እንወጣ” ዐውደ ርዕይ ተከፈተ
ሰኔ 28 ቀን 2006 ዓ.ም.
አውሮፓ ማእከል የጀርመን ቀጠና ማእከል
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የማኅበረ ቅዱሳን የአውሮፓ ማእከል የጀርመን ቀጠና ማእከል በፍራንክፈርት ከተማ ኢኮነን ሙዚየም ያዘጋጀው ዐውደ ርእይ ተከፈተ፡፡
ከሰኔ 27- 29 ቀን 2006 ዓ.ም./July 4-6, 2014/ እንዲታይ የተዘጋጀው ዐውደ ርእይ ጥሪ የተደረገላቸው ካህናትና ምእመናን በተገኙበት በልዩ ልዩ ዝግጅቶች ተከፍቷል፡፡ ጸሎተ ወንጌል በቦታው በተገኙ ካህናት ተደርጓል፤ የዐውደ ርእዩን የዝግጅት ሒደትና ይዘት አስመልክቶም አቶ ቃለ አብ ታደሰ የዝግጅት ኮሚቴው ሰብሳቢ የመክፈቻ ንግግር አድርገዋል፡፡
እንደ አቶ ቃለ አብ ገለጻ የጥንታዊቷንና የሐዋርያዊቷን ቤተ ክርስቲያን ታሪክ፣ ባሕልና ትውፊት ማስተዋወቅን ዓላማው ያደረገው ዝግጅቱ በሦስት ዋና ዋና ክፍሎች ተከፋፍሎ የተዘጋጀ ነው፡፡ የመጀመሪያው ክፍል የቤተ ክርስቲያኗን ታሪክ በአጭሩና ተመልካች በቀላሉ ሊረዳው በሚችለው መንገድ የቀረበበት የቤተ ክርስቲያን ታሪክ ነው፡፡ ሁለተኛው ደግሞ የዕውቀትና የጽድቅ እንዲሁም የልማት መሠረቶች የነበሩት ገዳማትና አድባራት እንዲሁም አብነት ት/ቤቶች ያደረጉትን አስተዋጽዖና በአሁኑ ወቅት እያጋጠማቸው ያለው ተግዳሮቶች በዝርዝር የቀረቡበት ነው፡፡ የመጨረሻው ደግሞ ከግንቦት 1984 ዓ.ም ጀምሮ ሰፊ መንፈሳዊና ማኅበራዊ አገልግሎቶችን ሲሰጥ የቆየውና ወደፊትም የሚሰጠው ማኅበረ ቅዱሳን ታሪክ፣ አገልግሎትና በየጊዜው ያጋጠሙት ችግሮች የቀረቡበት ክፍል ነው፡፡ ቤተ ክርስቲያን በአውሮፓ ያላት የአገልግሎት ታሪክ የተዳሰሰበት አንዱ የመርሐ ግብሩ አካል ነበር፡፡
በክብር እንግድነት ተገኝተው ዐውደ ርዕዩን በጸሎት የከፈቱት መልዐከ ፀሐይ ቆሞስ አባ ሲራክ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ምስራቅና ምዕራብ አውሮፓ ሀገረ ስብከት የፍራንክፈርት ደብረ ፀሐይ ቅድስት ማርያም ቤተ ክርስቲያን አስተዳዳሪ ናቸው፡፡ መልአከ ፀሐይ በመክፈቻ መርሐ ግብሩ ላይ የተከፈተው ዐውደ ርዕይ በፍራንክ ፈርት ከተማ ለአራተኛ ጊዜ እንደኾነ በማውሳት፤ ሁሉንም ዐውደ ርእዮች አዘጋጅቶ ለፍራንክፈርት ከተማና አካባቢው ሕዝብ ለዕይታ ያቀረበው በማኅበረ ቅዱሳን የጀርመን ቀጠና ማእከል ምስጋና ይገባዋል ብለዋል፡፡ ማኅበሩ ለቤተ ክርስቲያን እየሰጠ ያለው አገልግሎት ሰፊና ጠቃሚ ነው ያሉት መልአከ ፀሐይ ቆሞስ አባ ሲራክ፤ ለዚሁ ደግሞ እኔ ራሴ ምስክር ነኝ በማለት በቅርብ ጊዜ ወደ ኢትዮጵያ ሔደው ማኅበሩ በአቡነ ቶማስ ዘደብረ ሃይዳ ገዳም እያደረገ ያለውን የልማት እንቅስቃሴ በአብነት ጠቅሰዋል፡፡
የዐውደ ርእዩን መከፈት አስመልክቶ አስተያየት እንዲሰጡ የተጠየቁት ምእመናንም በዝግጅቱ እንደተደሰቱ ገልጸዋል፡፡ በፍራንክፈርት ከተማ ነዋሪ የኾኑት አቶ ነቢዩ የማነ፤ ላለፉት ሦስት ጊዜያት የቀረቡትን ዝግጅቶች እንደተመለከቱ አውስተው «ይኸኛውም ዝግጅት ብዙ ያላወኳቸውን ነገሮች አሳውቆኛል፡፡ ይልቁንም የቤተ ክርስቲያኗ ልጆች ምን ያህል ሓላፊነታችንን እንዳልተወጣን አስገንዝቦኛል፤ ይህም በእውነት ቁጭት ፈጥሮብኛል፡፡ ማኅበረ ቅዱሳን በሀገር ቤትም ይሁን በውጭ የሚሰጠው አገልግሎት በእጅጉ እየጠቀመን ነውና ሁሉም ቢደግፈው» በማለት ጥሪያቸውን አስተላልፈዋል፡፡
በተመሳሳይ ሁኔታም በከተማው ነዋሪ የኾኑት ወ/ሮ እጥፍ ወርቅ ወልዴ ባዩት ዝግጅት ብዙ ነገር እንዳወቁና «ሁሉም በውጭ የሚኖረው ምእመን በሀገራችን በችግር ላይ ያሉትን ገዳማትንና አድባራትን እንዲሁም አብነት ት/ቤቶችን ለዕረፍትም ይሁን ለልዩ ልዩ ጉዳዮች ወደ ሀገር ቤት ስንሔድ በአካል በመገኘት ልናያቸው ይገባል፤ አይተንም መርዳት ይጠበቅብናል፤» ብለዋል፡፡ አቶ ኤልያስ መሸሻ ደግሞ በስዊዘርላን ነዋሪ የኾኑና ዝግጅቱ ብቁ ቁም ነገሮችን እንዳሳወቃቸው ጠቅሰው፤ «ይህን መሰሉ ድንቅና ጠቃሚ ዝግጅት በሁሉም የአውሮፓ ከተሞች ተዘዋውሮ ሊታይ ይገባዋል» ብለዋል፡፡
እስከ እሑድ ሰኔ 29 ቀን 2006 ዓ.ም. /July 6, 2014/ ድረስ የሚቆየውና በበርካታ ምእመናንና ጀርመናውያን እንደሚጎበኝ የሚበሚጠበቀው በዚህ ዝግጅት ጥናታዊ ጽሑፎችና የቤተ ክርስቲያኗን ልዩ ልዩ ባሕሎች የሚያስተዋውቁ ትዕይንቶችና ስብከተ ወንጌል ይቀርባሉ፡፡
በሀገረ ጀርመን አስራ አንድ አብያተ ክርስቲያናት የሚገኙ ሲኾን ሁሉም በደቡብ ምስራቅና ምዕራብ አውሮፓ ሀገረ ስብከት ስር የታቀፉና አገልግሎት የሚሰጡ ናቸው፡፡ መንበረ ጵጵስናውን በፍራንክፈርት ከተማ ያደረገው ሀገረ ስብከቱ ሊቀ ጳጳስም ብፁዕ አቡነ ሙሴ ናቸው፡፡



ከሰሜን ሸዋ ሀገረ ስብከት ደብረ ብርሃን ከተማ በአሥር ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ ከሚገኘው የአጤ ዋሻ ደብረ ጽዮን ቅድስት ማርያም ቤተ ክርስቲያን ተዘርፎ ጅቡቲ ውስጥ ለ17 ዓመታት ተደብቆ የነበረው ታቦተ መድኃኔዓለም ወደ አዲስ አበባ ተመልሶ ሰኔ 21 ቀን 2006 ዓ.ም. ወደ መንበረ ክብሩ ገብቷል፡፡ /ሚያዚያ 17 ቀን 2006 ዓ.ም. ታቦቱ ከጅቡቲ ወደ አዲስ አበባ መግባቱን ከዚህ በፊት መዘገባችን ይታወሳል/
ሚያዚያ 17 ቀን 2006 ዓ.ም. ወደ አዲስ አበባ ተመልሶ በጠቅላይ ቤተ ክህነት የቅርስ ጥበቃና ቤተ መዘክር ለጊዜው እንዲቀመጥ በማድረግ፤ በቅዱስ ሲኖዶስ ውሳኔ ሰኔ 21 ቀን 2006 ዓ.ም. በከፍተኛ መንፈሳዊ ሥነ ሥርዓት ወደ አጤ ዋሻ ደብረ ጽዮን ቅድስት ማርያም ቤተ ክርስቲያን አሸኛኘት ተደርጎለታል፡፡
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የማኅበረ ቅዱሳን የአውሮፓ ማእከል የጀርመን ቀጠና ማእከል “ለሁለንተናዊ የቤተ ክርስቲያን እድገት የድርሻችንን እንወጣ” በሚል መሪ ቃል ልዩ ዐውደ ርዕይ፤ ዐውደ ጥናትና የስብከተ ወንጌል መርሐ ግብር በፍራንክፈርት ከተማ ኢኮነን ሙዚየም ከሰኔ 27- 29 ቀን 2006 ዓ.ም./July 4-6, 2014/ እንደሚካሔድ ቀጠና ማእከሉ አስታወቀ፡፡
ሠኔ 22 ቀን 2006 ዓ.ም በመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት የስብከተ ወንጌል አዳራሽ በተደረገው ጉባኤ ላይ የእንጦጦ ደብረ ኃይል ቅዱስ ራጉኤል ወኤልያስ ቤተ ክርስቲያን ሰበካ ጉባኤ ጽ/ቤት ለካህናት ደመወዝ ለመክፈል በመቸገሩ በቤተ ክርስቲያኑ ተገቢውን መንፈሳዊ አገልግሎት ለመስጠት ችግር እያጋጠመው መሆኑን ገለጠ፡፡
የቤተ ክርስቲያኑ አስተዳዳሪ አባ ወልደ መድኅን ተክለ ብርሃን የእንጦጦ ደብረ ኃይል ቅዱስ ራጉኤል ወኤልያስ ቤተ ክርስቲያንና የርዕሰ አድባራት እንጦጦ መንበረ ፀሐይ ቅድስት ማርያም ቤተ ክርስቲያን ከግቢያቸው አጥር ውጭ ምንም ይዞታ የሌላቸው በመሆኑ እና ቀደም ሲል የነበረው 270.9 ሄክታር ይዞታ በመነጠቁ ምክንያት አልምተን የገቢ ምንጭ የምንፈልግበት ሁኔታ የለም ሲሉ ተናግረዋል፡፡
ዓ.ም መጨረሻ ዐፄ ምኒልክ እንጦጦ ከተማ ከቆረቆሩ በኋላ፣ የልዑል እግዚአብሔርን ቤተ መቅደስ ለማሳነጽ በነበራቸው ምኞት ከደብረ ሊባኖስ ገዳም አባቶችን አስመጥተውና ቦታውን አስባርከው የእንጦጦ ደብረ ኃይል ቅዱስ ራጉኤል ወኤልያስ ቤተ ክርስቲያን ሊታነጽ መቻሉን ያገኘነው መረጃ ያመለክታል፡፡
ክርስቲያኑ ወደዚህ የተቀደሰ ቦታ በመምጣት፣ በመሳለምና የበኩላቸውን አስተዋጽኦ በማበርከት የበረከቱ ተሳታፊ ይሆኑ ዘንድ ጥሪያቸውን አስተላልፈዋል፡፡
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የሰዋስወ ብርሃን ቅዱስ ጳውሎስ መንፈሳዊ ኮሌጅ በመደበኛና በማታ መርሐ ግብር ትምህርታቸውን የተከታተሉ 212 ደቀመዛሙርትን በዲፕሎማ አስመረቀ፡፡
ከተመራቂ ደቀ መዛሙርቱ መካከል አባ ኪሮስ ወልደ አብ የትምህርት ቆይታቸውን አስመልክቶ የተሰማቸው ስሜት ሲገለጡ “ትምህርት ጀመርኩ እንጂ አልጨረስኩትም፤ የበለጠ እንድማር አነሳሥቶኛልና እቀጥልበታለሁ፡፡ በኮሌጁ ቆይታዬም በእቅድ መመራት በመቻሌ በጥሩ ሁኔታ ተምሬ በማዕረግ ለመመረቅ ችያለሁ” ብለዋል፡፡
ያለመሆን፤ ለመምህራን በቂ ደሞዝ ያለመከፈል፤ ከሌሎች መሰል የቤተ ክርስቲያኒቱ ኮሌጆች ጋር የልምድ ልውውጥ ያለማድረግ፤ በቤተ መጻሕፍቱ ውስጥ የሚገኙ መጻሕፍት በቂ ያለመሆናቸው፤ የመደበኛ ተማሪዎች ቁጥር መቀነስ እንደ ችግር ከጠቀሷቸው ውስጥ ይገኙበታል፡፡