የንባብ ባህልን ለማሳደግ ቤተ ክርስቲያን የሚኖራት ድርሻ ከፍተኛ መሆኑ ተገለጸ
ሐምሌ 1 ቀን 2006 ዓ.ም.
ይብረሁ ይጥና
ከፍተኛ ድር የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ትርጉም ያለው የንባብ ባሕልን ለማሳደግ ከፍተኛውን ድርሻ መያዝ እንደሚገባት በማኅበረ ቅዱሳን የጥናትና ምርምር ማእከል ባዘጋጀው የንባብ ባሕል አስመልክቶ በቀረበ የጥናት ጉባኤ ላይ ተገለጸ፡፡
ሠኔ 28 ቀን 2006 ዓ.ም. ለግማሽ ቀን በማኅበሩ ሕንፃ ላይ በተካሔደው ጉባኤ ትርጉም ያለው የንባብ ባሕል በዕውቀት እና በሥነ ምግባር የታነፀ ዜጋ ለማፍራት በሚል መሪ ቃል የተዘጋጀ ሲሆን፤ “የንባብ ባሕልን ለማሳደግ የተለያዩ አካላት ሚና” ፤ እንዲሁም “ትርጉም ያለው የንባብ ባሕል በኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን” በሚሉ ሁለት ርእሰ ጉዳች ላይ የተደረጉ ጥናቶች ቀርበዋል፡፡
በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ የአማርኛ ቋንቋ፤ ሥነ ጽሑፍና ፎክሎር መምህር የሆኑት መምህር ደረጀ ገብሬ “የንባብ ባህል ለማሳደግ የተለያዩ አካላት ሚና” በሚል ርእስ ባቀረቡት ጥናት፤ የንባብ ምንነት፤ የንባብ ክሂል የእድገት ደረጃዎች፤ የማንበብ ጠቃሚነት፤ የማንበብ ባሕልን የማሳደግና የማዳበሪያ ሥልቶቹ ምን እንደሆኑ በስፋት ዳስሰዋል፡፡ በተለይም ሕፃናት የቋንቋ ችሎታቸውን በማዳበር በየጊዜው የማዳመጥና የማንበብ ፍላጎታቸውን ማሳደግ እንደሚቻል ገልጠዋል፡፡
ለንባብ ባሕል መዳበር ትምህርት ቤቶችና ወላጆች፤ መንግሥትና መንግሥታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች ትኩረት ሠጥተው መሥራት እንደሚገባቸውም በጥናታቸው አመልክተዋል፡፡ “ትርጉም ያለው የንባብ ባህል በኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን” በሚል ርእስ ጥናታቸውን ያቀረቡት አቶ ጸጋዘአብ ለምለም ደግሞ ትርጉም ያለው የንባብ ባሕል ለፈጣሪነት፤ ለውጤታማነት፤ ለብቁ ተወዳደሪነትና ለሀገር ሁለንተናዊ ብልጽግና ጠቀሜታው የጎላ መሆኑን ጠቁመዋል፡፡
ዓለም አቀፋዊት የሆነችው ቅድስት ቤተ ክርስቲያን የብዙ መጻሕፍትና መዛግብት እንዲሁም ቅርሶች ባለቤት እንደመሆኗ መጠን አገልግሎቷን ካለንባብ ማሰብ አስቸጋሪ እንደሚያደርገው አመልክተው፤ ቤተ ክርስቲያን በርካታ ምሥጢራት እንዳሏት ሁሉ እነዚህን ምሥጢራት ለአገልግሎት ለማብቃት ትርጉም ያለው የንባብ ባሕል አስፈላጊነትና ንባብ የቤተ ክርስቲያኗ አንዱ አካል መሆኑን በጥናታቸው ዳስሰዋል፡፡
ንባብ ሲባል ከፊደል ቆጠራ ጀምሮ ያለው ሲሆን፤ ቤተ ክርስቲያን የፊደል ባለቤት ሆና ብትቀጥልም ትርጉም ያለው የንባብ ባሕል አድማሷን አለማስፋፋቷን በስፋት አቅርበዋል፡፡ የዐቅም ማጣት ሳይሆን ዐቅምን አለማወቅ፤ የአጠቃቀም ችግር፤ ተቋማዊ የሆነ አስተዳደር አለመዘርጋት፤ ቤተ ክርስቲያን ከዘመኑ ቴክኖሎጂ ጋር አለመተሳሰሯ፤ ንባብን እንደ አንድ የአገልግሎት አካል አለመመልከት እንደ ምክንያትነት ተጠቅሰዋል፡፡
ቤተ ክርስቲያን ትርጉም ያለው የንባብ ባሕል አድማስን ለማስፋፋት ንባብን እንደ ሃይማኖታዊ በዓል አከባበራችን ባሕል ማድረግ፤ ዐቅምን ማሳደግና ማበልጸግ፤ ጠንካራ ተቋማዊ አስተዳደርን መዘርጋት፤ ከዘመኑ ቴክኖሎጂ ጋር ማስተሳሰር፤ የጥናትና ምርምር ማእከላትን ማበራከት የመሳሰሉትን ጥናት አቅራቢው እንደ መፍትሔ አቅርበዋል፡፡
በቀረቡት ሁለቱም ጥናታዊ ጽሑፎች ላይ ከተሳታፊዎች ጥያቄዎች ቀረበው በባለሙያዎቹ ማብራሪያ ተሰጥቶባቸዋል፡፡



በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የቅድስት ሥላሴ መንፈሳዊ ኮሌጅ በቀንና በማታ መርሐ ግብር ያስተማራቸውን ሦስት መቶ ደቀመዛሙርት አስመረቀ፡፡



በክብር እንግድነት ተገኝተው ዐውደ ርዕዩን በጸሎት የከፈቱት መልዐከ ፀሐይ ቆሞስ አባ ሲራክ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ምስራቅና ምዕራብ አውሮፓ ሀገረ ስብከት የፍራንክፈርት ደብረ ፀሐይ ቅድስት ማርያም ቤተ ክርስቲያን አስተዳዳሪ ናቸው፡፡ መልአከ ፀሐይ በመክፈቻ መርሐ ግብሩ ላይ የተከፈተው ዐውደ ርዕይ በፍራንክ ፈርት ከተማ ለአራተኛ ጊዜ እንደኾነ በማውሳት፤ ሁሉንም ዐውደ ርእዮች አዘጋጅቶ ለፍራንክፈርት ከተማና አካባቢው ሕዝብ ለዕይታ ያቀረበው በማኅበረ ቅዱሳን የጀርመን ቀጠና ማእከል ምስጋና ይገባዋል ብለዋል፡፡ ማኅበሩ ለቤተ ክርስቲያን እየሰጠ ያለው አገልግሎት ሰፊና ጠቃሚ ነው ያሉት መልአከ ፀሐይ ቆሞስ አባ ሲራክ፤ ለዚሁ ደግሞ እኔ ራሴ ምስክር ነኝ በማለት በቅርብ ጊዜ ወደ ኢትዮጵያ ሔደው ማኅበሩ በአቡነ ቶማስ ዘደብረ ሃይዳ ገዳም እያደረገ ያለውን የልማት እንቅስቃሴ በአብነት ጠቅሰዋል፡፡
ከሰሜን ሸዋ ሀገረ ስብከት ደብረ ብርሃን ከተማ በአሥር ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ ከሚገኘው የአጤ ዋሻ ደብረ ጽዮን ቅድስት ማርያም ቤተ ክርስቲያን ተዘርፎ ጅቡቲ ውስጥ ለ17 ዓመታት ተደብቆ የነበረው ታቦተ መድኃኔዓለም ወደ አዲስ አበባ ተመልሶ ሰኔ 21 ቀን 2006 ዓ.ም. ወደ መንበረ ክብሩ ገብቷል፡፡ /ሚያዚያ 17 ቀን 2006 ዓ.ም. ታቦቱ ከጅቡቲ ወደ አዲስ አበባ መግባቱን ከዚህ በፊት መዘገባችን ይታወሳል/
ሚያዚያ 17 ቀን 2006 ዓ.ም. ወደ አዲስ አበባ ተመልሶ በጠቅላይ ቤተ ክህነት የቅርስ ጥበቃና ቤተ መዘክር ለጊዜው እንዲቀመጥ በማድረግ፤ በቅዱስ ሲኖዶስ ውሳኔ ሰኔ 21 ቀን 2006 ዓ.ም. በከፍተኛ መንፈሳዊ ሥነ ሥርዓት ወደ አጤ ዋሻ ደብረ ጽዮን ቅድስት ማርያም ቤተ ክርስቲያን አሸኛኘት ተደርጎለታል፡፡
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የማኅበረ ቅዱሳን የአውሮፓ ማእከል የጀርመን ቀጠና ማእከል “ለሁለንተናዊ የቤተ ክርስቲያን እድገት የድርሻችንን እንወጣ” በሚል መሪ ቃል ልዩ ዐውደ ርዕይ፤ ዐውደ ጥናትና የስብከተ ወንጌል መርሐ ግብር በፍራንክፈርት ከተማ ኢኮነን ሙዚየም ከሰኔ 27- 29 ቀን 2006 ዓ.ም./July 4-6, 2014/ እንደሚካሔድ ቀጠና ማእከሉ አስታወቀ፡፡
ሠኔ 22 ቀን 2006 ዓ.ም በመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት የስብከተ ወንጌል አዳራሽ በተደረገው ጉባኤ ላይ የእንጦጦ ደብረ ኃይል ቅዱስ ራጉኤል ወኤልያስ ቤተ ክርስቲያን ሰበካ ጉባኤ ጽ/ቤት ለካህናት ደመወዝ ለመክፈል በመቸገሩ በቤተ ክርስቲያኑ ተገቢውን መንፈሳዊ አገልግሎት ለመስጠት ችግር እያጋጠመው መሆኑን ገለጠ፡፡
የቤተ ክርስቲያኑ አስተዳዳሪ አባ ወልደ መድኅን ተክለ ብርሃን የእንጦጦ ደብረ ኃይል ቅዱስ ራጉኤል ወኤልያስ ቤተ ክርስቲያንና የርዕሰ አድባራት እንጦጦ መንበረ ፀሐይ ቅድስት ማርያም ቤተ ክርስቲያን ከግቢያቸው አጥር ውጭ ምንም ይዞታ የሌላቸው በመሆኑ እና ቀደም ሲል የነበረው 270.9 ሄክታር ይዞታ በመነጠቁ ምክንያት አልምተን የገቢ ምንጭ የምንፈልግበት ሁኔታ የለም ሲሉ ተናግረዋል፡፡
ዓ.ም መጨረሻ ዐፄ ምኒልክ እንጦጦ ከተማ ከቆረቆሩ በኋላ፣ የልዑል እግዚአብሔርን ቤተ መቅደስ ለማሳነጽ በነበራቸው ምኞት ከደብረ ሊባኖስ ገዳም አባቶችን አስመጥተውና ቦታውን አስባርከው የእንጦጦ ደብረ ኃይል ቅዱስ ራጉኤል ወኤልያስ ቤተ ክርስቲያን ሊታነጽ መቻሉን ያገኘነው መረጃ ያመለክታል፡፡
ክርስቲያኑ ወደዚህ የተቀደሰ ቦታ በመምጣት፣ በመሳለምና የበኩላቸውን አስተዋጽኦ በማበርከት የበረከቱ ተሳታፊ ይሆኑ ዘንድ ጥሪያቸውን አስተላልፈዋል፡፡
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የሰዋስወ ብርሃን ቅዱስ ጳውሎስ መንፈሳዊ ኮሌጅ በመደበኛና በማታ መርሐ ግብር ትምህርታቸውን የተከታተሉ 212 ደቀመዛሙርትን በዲፕሎማ አስመረቀ፡፡
ከተመራቂ ደቀ መዛሙርቱ መካከል አባ ኪሮስ ወልደ አብ የትምህርት ቆይታቸውን አስመልክቶ የተሰማቸው ስሜት ሲገለጡ “ትምህርት ጀመርኩ እንጂ አልጨረስኩትም፤ የበለጠ እንድማር አነሳሥቶኛልና እቀጥልበታለሁ፡፡ በኮሌጁ ቆይታዬም በእቅድ መመራት በመቻሌ በጥሩ ሁኔታ ተምሬ በማዕረግ ለመመረቅ ችያለሁ” ብለዋል፡፡
ያለመሆን፤ ለመምህራን በቂ ደሞዝ ያለመከፈል፤ ከሌሎች መሰል የቤተ ክርስቲያኒቱ ኮሌጆች ጋር የልምድ ልውውጥ ያለማድረግ፤ በቤተ መጻሕፍቱ ውስጥ የሚገኙ መጻሕፍት በቂ ያለመሆናቸው፤ የመደበኛ ተማሪዎች ቁጥር መቀነስ እንደ ችግር ከጠቀሷቸው ውስጥ ይገኙበታል፡፡