“ስለ ሃይማኖታችንና ስለ ቤተ ክርስቲያናችን ዘብ የምንቆምበት ወቅት አሁን ነው”
/ብፁዕ አቡነ ሉቃስ/
ኅዳር 26 ቀን 2007 ዓ.ም.
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን በታሪክ ከገጠሟት ልዩ ልዩ ፈተናዎች ይልቅ በዚህኛው ትውልድ የደረሰባት ፈተና (ሙስናና ብልሹ አሠራር፤ የመልካም አስተዳደር እጦት፣ በውጭ ካሉ አባቶች ጋር ያልተቋጨው ዕርቀ ሰላም) ወደ ፊት እንዳትራመድ አድርጓታል፡፡ በእርግጥ የቤተ ክርስቲያኒቱ ወቅታዊ ችግሮች እነዚህ ብቻ ናቸው ማለት አይደለም፡፡ ችግሮችን ከማውራት ይልቅ መፍትሔው ላይ ማተኮር ለቤተ ክርስቲያኒቱም ለመንጋውም ጠቃሚ ስለሚሆን ነው እንጂ፡፡
በዚህ ሒደት የቤተ ክርስቲያኒቱን ሃይማኖታዊና አስተዳደራዊ ችግሮች በጥልቀት እየተወያየ መፍታሔ የሚሰጠው ቅዱስ ሲኖዶስ በዘንድሮው ጥቅምት 2007 ዓ.ም ባካሔደው ጉባኤ ብዙ ደስ የሚያሰኙ ውሳኔዎችን አሳልፏል፡፡ ይህንና ሌሎች ተያያዥ ጉዳዮችን አስመልክተን የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊና የሰቲት ሑመራ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ከሆኑት ከብፁዕ አቡነ ሉቃስ ጋር ያደረግነውን ቃለ ምልልስ እንደሚከተለው አቅርበነዋል፡፡
የሠላሳ ሦስተኛው አጠቃላይ ሰበካ መንፈሳዊ ጉባኤ በቅዱስ ሲኖዶስ እይታ ምን ይመስል ነበር?
የሠላሳ ሦስተኛው አጠቃላይ ሰበካ መንፈሳዊ ጉባኤ በአህጉረ ስብከት፣ በድርጅቶች፣ በልማት ተቋማት ከፍተኛ ለውጥ የታየበት፣ በማኅበራዊና በሰብአዊ እንቅስቃሴም መልካም ነገሮች የታየበት ነው፡፡ ዕድገት ነበረው፤ ለውጥ ነበረው፡፡ ይሁን እንጂ በስብሰባው ላይ አላስፈላጊ የሆኑ ጎኖች ነበሩት፡፡ ይህም ጥቂት የሚባሉ ታዛቢ ግለሰቦች የፈጠሩት ሁካታ፤ አግባብነት የሌለው ጥያቄ ነው፡፡ ቅዱስ ሲኖዶስ ይህን ክፍተት እንደ እጥረት በማየት እርምት እንዲሰጥ በምልዓተ ጉባኤው ወስኗል፡፡
ወደፊትም እንዲህ አይነት ችግር እንዳይፈጠር ቃለ ዐዋዲው፤ ሕገ ቤተ ክርስቲያኑ በሚያዘው መሠረት ጉባኤው የሚመለከታቸው ተሳታፊዎችና ታዛቢዎች ቦታ ቦታቸውን ይዘው እንዲቀመጡ ይሆናል፡፡ በጋራ መግለጫው የተወሰኑትንና ቅዱስ ሲኖዶስ እርምት እንዲሰጥባቸው የወሰነባቸውን ተግባራት መፈጸምና አለመፈጸማቸውን ክትትል የሚያደርጉ ቋሚ ሲኖዶስ፣ ጠቅላይ ቤተ ክህነት፣ የአህጉረ ስብከት ሊቃነ ጳጳሳት ናቸው፡፡
ቅዱስ ሲኖዶስ ጊዜ ወስዶ በጥልቀት የተወያየባቸው ነጥቦች ምን ምን ናቸው?
የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ የውይይት አጀንዳዎች አጠቃላይ 21 ነበሩ፡፡ በውይይቱ ወቅት ሰፊ ጊዜ የወሰደው አንደኛው አጀንዳ የተረቀቀው ሕገ ቤተ ክርስቲያን ነው፡፡ መወያያ አሳቡም ሊቃነ ጳጳሳቱ ተጠሪነታቸው ለማን ይሁን የሚለው ጉዳይ ነበር፡፡ የፊተኛው ሕገ ቤተ ክርስቲያን ለቅዱስ ሲኖዶስ ይላል፡፡ አሁን ግን ሊቃነ ጳጳሳቱ ተጠሪነታቸው ለፓትርያርኩና ለቅዱስ ሲኖዶስ የሚል አሳብ ተነሥቶ ሰፊ ውይይት ከተደረገ በኋላ ሐዋርያት ተጠሪነታቸው ለአንዱ እግዚአብሔር ነው፡፡ የጉባኤው መሪ መንፈስ ቅዱስ ነው፡፡ በፊትም አሁንም ሊቃነ ጳጳሳቱን የሚሾመው ቅዱስ ሲኖዶስ ነው፡፡ ስለዚህ የሊቃነ ጳጳሳት ተጠሪነት በፊት በነበረው እንዲቀጥል በአንድ ድምፅ ተስማምተዋል፡፡
ከዚሁ ጋር ተያይዞ የሊቃነ ጳጳሳት ዝውውርም ተነሥቷል፡፡ ሊቃነ ጳጳሳትን ማዘዋወር የሚችለው ቋሚ ሲኖዶሱ መሆን እንዳለበት ምልዓተ ጉባኤው ወስኗል፡፡ ለሃይማኖት፣ ለሥርዓት፣ ለምእመናንና ለሀገሪቱ የሚጠቅሙ ብዙ አሳቦች በሕገ ቤተ ክርስቲያኑ እንዲካተቱ ተደርጓል፡፡
ሁለተኛው የማኅበራት ጉዳይ ነው፡፡ በልዩ ልዩ አገልግሎቶች በማኅበር ስም ተደራጅተው ቤተ ክርስቲያንን የሚያገለግሉ ማኅበራት በምን መልኩ በቤተ ክርስቲያኒቱ መዋቅር ሥር ይሁኑ በሚለው ምልዓተ ጉባኤው በስፋት ተወያይቷል፡፡ እገሌ ጥሩ ነው እገሌ መጥፎ ነው የተባለ ማኅበር የለም፡፡ ልጆቻችን ለቤተ ክርስቲያናችን አገልግሎት ጠቃሚዎች ናቸው፤ መጀመሪያ ሰዎች ለቤተ ክርስቲያን ያስፈላጓታል በማለት ደስ ደስ የሚሉ አሳቦች ተነሥተዋል፡፡ በዚህም የልጆቻችን አገልግሎት ጠቃሚ እንደሆነ የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ በደንብ አምኖበታል፡፡
ልጆቻችንን ማቅረብና መውደድ እንደሚገባም ሁሉም ተስማምቷል፡፡ ስለዚህ ማኅበራት በሙሉ ተጠሪነታቸው ለሰንበት ትምህርት ቤቶች ማደራጃ መምሪያ እንዲሆን ተወስኗል፡፡ ገቢያቸውንና ወጭያቸውን ቤተ ክርስቲያኒቱ በምትጠቀማቸው ሞዴላ ሞዴሎች እንዲጠቀሙ ተወስኗል፡፡
ማኅበረ ቅዱሳንስ?
በማኅበረ ቅዱሳንም ላይ የተለየ አቋም የለም፡፡ ልጆቻችን፤ አገልግሎታቸው በጣም ጠቃሚ ነው፡፡ በቤተ ክርስቲያን እያሳየ ያለው ተግባር ጠቃሚ ነው፤ ገደማትን፣ የአብነት ትምህርት ቤቶችንና ሌሎች ልማቶችን በተመለከተ ማንኛውንም ሥራ በአጋርነት እየሠራ ያለ ትልቅ ማኅበር መሆኑን ምልዓተ ጉባኤው አምኗል፡፡ እንዲያውም ምሁራን ያሉበት፣ ለቤተ ክርስቲያን፣ ለሃይማኖት፣ ለሥርዓት፣ ለሀገር፣ ለልማት የሚጠቅሙ ሰዎች ያሉበት ነው የሚሉ ትልልቅ አሳቦች ተነሥተዋል፡፡ ወደ ፊትም የቤተ ክርስቲያን ጠበቃ ሆኖ እንደሚቀጥል ታምኖበታል፡፡
ማኅበረ ቅዱሳንን በተመለከተ ምልዓተ ጉባኤው በአንድ ድምፅ በዚህ መልክ ነው የተረዳው፡፡ ለአሁኑ ቀድሞ ወደ ነበረበት ሰንበት ትምህርት ቤቶች ማደራጃ መምሪያ ሥር ሆኖ ተጠሪነቱ ግን ለማደራጃ መምሪያው ሊቀ ጳጳስ እንዲሆን ተወስኗል፡፡ ቁጥጥሩን፣ ግምገማውንና ክትትሉን የሚያደርገው ደግሞ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ነው፡፡
የማኅበራት ሕግ ሲወጣም እንደ ማኅበረ ቅዱሳን ያሉት ማኅበራት ክፍል “ሀ”፣ ሌሎች ማኅበራት ክፍል “ለ” በሚል አደረጃጀት ሥርዓት እንዲይዝ ይደረጋል የሚል እምነት አለኝ፡፡ ገንዘቡን በቤተ ክርስቲያኒቱ ሞዴላ ሞዴሎች እየተጠቀመ ለሚፈለገው አገልግሎት እንዲውል በሚል ተወስኗል፡፡ ገንዘቡ ለምን ለምን አገልግሎት እንደ ዋለ መከታተል እንጂ ወደ ቤተ ክርስቲያን የሚመጣ የለም፡፡ ቅዱስ ሲኖዶስ በጥልቀት አይቶ በስፋት ተመልክቶ አስደሳች በሆነ መልኩ የወሰነው ይኼን ነው፡፡
ሌላው ስለ ሰላም ነው፡፡ ያለ ሰላም እግዚአብሔርን ማየት አይቻልም እንዲል ቅዱስ ጳውሎስ በውጭ ያለው ዕርቀ ሰላም እንዲቀጥል ተወስኗል፡፡ ዝርዝር ሁኔታው ወደፊት የሚወሰን ይሆናል፡፡
የቅዱስ ሲኖዶስ አጀንዳዎች 21 ሆነው ሳለ በመግለጫው ግን 9ኙ ብቻ ነበር እንዲካተቱ የተደረገው፣ ለምን?
የዚህ ምክንያት ቅዱስ ሲኖዶስ ለዓለም መገለጽ የነበረባቸውን ለይቶ ነው መግለጫ የሰጠው፡፡ ሌላው የቤተ ክርስቲያኒቱ የውስጥ አሠራር ስለሆነ ውሳኔዎቹ ተለይተው ነው የቀረቡት፡፡
ሙስና ቤተ ክርስቲያኗን ምን ያህል ነው የጎዳት?
ያለፉትን ጊዜያት ጨምሮ አሁን ቤተ ክርስቲያን ያለችበትን ሁኔታ ስናይ በሙሰኞች እየታመሰች ትገኛለች፡፡ ቤተ ክርስቲያኗ ስሟ በማይገባ (በሙስና) እንዲጠራ አድርገዋል፡፡ የእነዚህ ሰዎች ማንነት ሲፈተሸ ደግሞ በቤተ ክርስቲያን ውስጥ ያሉ ነገር ግን የቤተ ክርስቲያን ሰዎች ያልሆኑ ገንዘቧን እንደፈለጉ የሚጠቀሙ ናቸው፡፡ በሌላ በኩል ቤተ ክርስቲያኗ የመልካም አስተዳደር ባለቤት እንዳትሆን በተለያየ ስልት ሲያከሽፉ ቆይተዋል፡፡ በተለይ ችግሩ እንደመዥገር ተጣብቆ ያለው አዲስ አበባ ላይ ነው፡፡
በቤተ ክህነቱ ቀልጣፋና ዘመናዊ አሠራር እንዳይሰፍንና ሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያን የማይገባቸውን ቦታ ስም እንዲሰጣቸው አድርጓል፡፡ የችግሩ ስፋት በዚህ አያበቃም፡፡ ቤተ ክርስቲያኒቱን በዘረኝነትና በጎጠኝነት እንድትተበተብ የፈጠረው ቁርሾ ከባድ ነው፡፡ ገጠር ብትሔድ እንዲህ ዓይነት ችግር የለም፡፡
ካህኑም ምእመኑም ጉቦ አይሰጥም፣ አይቀበልም፡፡ ችግሩ ያለው አዲስ አበባ ዙሪያ ነው፡፡ ለሕዝቡም እየነገርን ከርመናል፤ አንተ ሕዝብ ገንዘብህን ጠብቅ!፤ አንተ ወጣት ቤተ ክርስቲያኗን ከነጣቂዎች ጠብቅ! እኛ ማስተማር ስላለብን ስንናገር ከርመናል፡፡
እንደ እውነቱ እኮ እኛ እየመራናቸው፣ ሰንበት ተማሪዎቻችን ጠንካራ ቢሆኑ ኖሮ ከሰባክያን፣ ከቀሳውስትና ከማኅበራት ጋር ተባብረው ሙስናን ከቤተ ክርስቲያን ለማጥፋት ይበቁ ነበር፡፡ በደንብ ተደራጅተው ገንዘቧን የሚበሉትን መቆጣጠር ይችሉ ነበር፡፡ ሌባ ፈሪ ነው፤ ሌባ ግንባር ለግንባር አይዋጋም፡፡ በሙዳየ ምፅዋቱ ብቻ ታጥረው ቀሩ እንጅ እንደቅዳቸው ቢሆንማ ቤተ ክርስቲያኗን ያጠፏት ነበር፤ ግን አልሆነላቸውም፡፡
ወደ ፊት ሙስናን ከቤተ ክርስቲያኒቱ ለማጥፋት ምን የተጀመረ እንቅስቃሴ አለ?
ይህ የሚያበቃበት ጊዜ በቅርብ ቀን እንደሚሆን እምነት አለኝ፡፡ ሙስና ይቁም እያልን ሁሉ ጊዜ ስንጮህ ቆይተናልና፡፡ መጀመሪያ መሣሪያ ይዞ ማስወጣት ሳይሆን ማስተማር ስላለብን ቀደም ብለን እያንዳንዱ ምእመን እስኪሰርጸው ድረስ እያስተማርን ነው፡፡ አሁን ግን በአባቶቻችን ሊቃውንት እየተረቀቀ ያለው መሪ እቅድ ሲጠናቀቅ የሙሰኞች ሰንሰለት ይበጣጠሳል ብለን እናምናለን፡፡ ምክንያቱም መሪ ዕቅዱ ለካህናቱ፣ ለሰበካ ጉባኤው፣ ለሰንበት ተማሪዎች፣ ለማኅበራቱ ከፍተኛ አቅም ይፈጥርላቸዋል፡፡ እነዚህ አካላት ተባብረው ከሠሩ ቤተ ክርስቲያን ከሙስና ትጸዳለች፡፡
በዚህ አሠራር ሁሉም የድርሻውን ከተወጣ የሚፈለገው ለውጥ ይመጣል ባይ ነኝ፡፡ በመሪ ዕቅዱ ካህኑ፣ አለቃው፣ ሒሳብ ሹሙ፣ ፀሐፊው እስከ የት ድረስ ነው ሓላፊነታቸው፣ የተቆጠረው ገንዘብ መዋል ማደር ያለበት የት ነው፤ ገንዘብ ቆጠራው ላይ ማን ይገኝ እና ሌሎች አሳቦች ይካተታሉ፡፡ ቤተ ክርስቲያኒቷ በምእመናን እጅ፣ በካህናት እጅ ስትሆን ነው ትክክል የምትመጣው፡፡ አለበለዚያ. . . ቤተ ክርስቲያኒቱን ባዶ ያደርጓታል፡፡ ይህ መቆም አለበት፡፡ እስከዛው ግን እያስተማርን እንደሆነ ሙሰኞች ይወቁት፡፡
ይልቅስ?
ቤተ ክርስቲያኒቷ ገና ያልሠራቻቸው ብዙ የቤት ሥራዎች አሉባት፡፡ ይህንን ነው መሥራት፡፡ ቤተ ክርስቲያን ብዙ የልማት ሥራዎች ያስፈልጓታል፡፡ በበቂ ሁኔታ የረዳናቸው ገዳማትና የአብነት ትምህርት ቤቶች የታሉ?፣ የምናሳድጋቸው ዕጓለማውታ ሕፃናት የታሉ? የታለ አረጋውያንን የምንጦረው? ስብከተ ወንጌል ያልተዳረሰባቸውን ጠረፋማ አካባቢዎች የታለ አስተምረን ያስጠመቅናቸው? ቤተ መጻሕፍት አዳራሽ የት ነው ያለው?፤
መኪና ጋራዥ ገብቶ ሲለወጥ እኛ ግን ሰውን የምንለውጥበት መንፈሳዊ ጋራዥ የት ነው ያለው? ስለዚህ የሰንበት ትምህርት ቤት ወጣቶች፣ ማኅበራት፣ አባቶት ካህናት እንደዚሁም ደግሞ ከላይም ከታችም ያሉ ምእመናን በሙሉ መጀመሪያ ትኩረታቸው ስለ ቤተ ክርስቲያን እምነትና ሥርዐት፣ ስለ ልማት፣ ስለ አንድነትና ስለ ፍቅር መሆን ይገባዋል፡፡ አበክሬ የምገልጸው የእምነታቸው፣ የሥርዓታቸው፣ የታሪካቸው፣ የሀገራቸው ፍቅር እንዲኖራቸውና ለሃይማኖታቸውና ለሀገራቸው ጠበቃ እንዲሆኑ ነው፡፡
በተለይ ማኅበራት፡- በአሁኑ ጊዜ ቁጥራቸው ቀላል የማይባሉ ማኅበራት አሉ፡፡ መጀመሪያ ቤተ ክርስቲያንን ማስቀደም አለባቸው፡፡ የእኔ መኖር ለቤተ ክርስቲያን ምን ጠቀመ? ማለት አለባቸው፡፡ ወደ ቤተ ክርስቲያን ተጠግተው የእኔ ድርሻ ምን መሆን አለበት ብለው አባቶችን በመጠየቅ መሥራት ይኖርባቸዋል፡፡ በአሁኑ ወቅት ሁሉም ሰው ለቤተ ክርስቲያን ዘብ መቆም አለበት፡፡ ይህቺ ጥንታዊትና ሐዋርያዊት የሆነች ቤተ ክርስቲያናችን እና አንጋፋ ሀገራችን በልጆቿ ማፈር የለባትም፤ ሌቦች ጥቂት ሆነው ብዙዎች ደጅ ሆነው ሲመለከቱ ያሳፍራል፣ በቤተ ክርስቲያኒቷ ሙስና አለ ማለት ያሳፍራል፣ በቤተ ክርስቲያን ድሆች ሲጦሩ፣ ልጆች ሲማሩ፣ መጻሕፍት ሲነበቡ አለማየት ያሳፍራል፡፡ ስለዚህ በአንድነት ስለቤተ ክርስቲያን ዘብ የምንቆምበት ጊዜ አሁን ነው፡፡
በቤተ ክርስቲያኒቷ አሁን ያለው እጥረት ተቀራርቦ አለመሥራት፤ አለ መወያየት ነው፡፡ እኛ በአብዛኛው ያሳለፍነው በመወነጃጀል ነው፡፡ ይሄ ደግሞ አየነው የት እንዳደረሰን፡፡ አንዱ አንዱን ሲወነጅል ቤተ ክርስቲያኗን ምን ያህል እንደጎዳት፤ ምን ያህል እሞት አፋፍ እንዳደረሳት ባለፉት ጊዜያት አይተነዋል፡፡ ሁሉም በየራሱ የሚሔድ ከሆነ በጎ አይሆንም፡፡ ተቀራርቦ መሥራት ያስፈልጋል፡፡ ትልቅ የመቀራረብ ሥራ መሠራት አለበት፡፡
በአባቶቻችን መሪነት አንድ ሆነን አንተ በዚህ ዝመት፤ አንተ በዚህ ሒድ መባባል ይቻላል፡፡ እንደ ገበሬ አረሙን ወደ ውጭ እየጣሉ፣ የወደቀውን ሰው እያነሡ መሔድ ይቀረናል፡፡ ተቀራርቦ አለመተቻቸትም ይቀረናል፡፡ ጥሩ ወተት ለማግኘት እላሟ ሥር ያለውን መዥገር መንቀል ያስፈልጋል፡፡ ሁሉም በየራሱ መቅረት መተው አለበት፡፡ አሁንም ጊዜው አለ ተቀራርበን እንሥራ ነው የምንለው፡፡ ምእመናንን ከተኩላዎች፣ ከነጣቂዎች መጠበቅ አለብን፡፡
በተጠራጣሪዎችና አማኝ ባልሆኑ አካላት የሚነገር፣ ቤተ ክርስቲያንን የሚመለከት ዘለፋ ከቀያጮች፣ ከበራዦች፣ ከስም አጥፊዎች የሚላኩ የኑፋቄ ቃላትን አለመቀበል ነው፡፡ የዘመኑን መሣሪያ ተጠቅመው ቤተ ክርስቲያንን ለማጥፋት የሚተጉ ተቃዋሚዎች ብዙዎች ናቸው፡፡ እነዚህን መቃወም መቻል አለብን፡፡ ሌላው ሥርዓቱንና ትውፊትን መጠበቅ ነው፡፡ ኦርቶዶክሳዊ የሆነው ሥርዓቱን እያከበረ ሌሎችን ይወዳል፣ እምነታችን ሁል ጊዜ የአንድነት፣ የሰላም ምልክት ናት፡፡ መሠረታችን ፍቅር ነው፡፡ ቃሉ ሰውን ውደድ ስለሆነ በዚህ እንትጋ ነው የምለው፡፡
ምንጭ፤- ስምዐ ጽድቅ ዘኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ኅዳር 1-15 ቀን 2007 ዓ. ም.



በማኅበረ ቅዱሳን የባሕር ዳር ማእከል በደብረ ጽዮን ሰላም አድርጊው ማርያም ገዳም በተሠጠው ቦታ በመገንባት ላይ የሚገኘው ጽሕፈት ቤት በቅርቡ እንደሚጠናቀቅ የጽ/ቤት ግንባታ ኮሚቴ የቴክኒክ ክፍል አስተባባሪ አቶ አስናቀ ለወየ አስታወቁ፡፡
ማኅበረ ቅዱሳን በቅዱሳት መካናት ልማትና ማኅበራዊ አገልግሎት አማካይነት በምሥራቃዊ ትግራይ ሀገረ ስብከት በደብረ ገሪዛን ጉንዳጉንዲ ቅድስት ማርያም፤ በሰሜን ምዕራብ ትግራይ ሽሬ እንዳሥላሴ ሀገረ ስብከት በአስገደ ጽምባላ ወረዳ በአቡነ ቶማስ ደብረ ማርያም ዘሃይዳ፤ በምሥራቃዊ ትግራይ ሀገረ ስብከት በማቅናት አጽቢ ወምበርታ ወረዳ በደብረ ቅዱሳን ዲቦ ቅድስት ማርያም አንድነት ገዳማት ያከናወናቸውን ፕሮጀክቶች አስመረቀ፡፡
ገዳሙ ያለበትን ችግር በማጥናት የውኃ ፕሮጀክቱን ተግባራዊ ለማድረግ ከፍተኛ ጥረት የተደረገ ሲሆን፤ መንገዱ በጣም አስቸጋሪና ከ3-4 ሰዓት በእግር የሚያስኬድ በመሆኑ አባቶች በሸክም፤ እንዲሁም ግመሎችን በመጠቀም የግንባታ ቁሳቁስ በማመላለስ ፕሮጀክቱን ለማጠናቀቅ ተችሏል፡፡
በምሥራቃዊ ትግራይ ሀገረ ስብከት ከተጠናቀቁት ፕሮጀክቶች መካከል አንዱ ደግሞ ለደብረ ገሪዛን ጉንዳጉንዲ ቅድስት ማርያም አንድነት ገዳም የተገነባው ሁለገብ ሕንፃ ነው፡፡ ሁለገብ ሕንፃው በአዲግራት ከተማ የተገነባ ሲሆን፤ ለተለያየ አገልግሎት በማከራየት ገቢ ማስገኘት የሚችል ነው፡፡ ሕንፃው በብር 2,326,717.87 /ሁለት ሚሊዮን ሦስት መቶ ሃያ ስድስት ሺሕ ሰባት መቶ ዐሥራ ሰባት ብር ከ87 ሣንቲም/ ተገንብቶ የርክክብ ሥነ ሥርዓቱ ተከናውኗል፡፡
በተጨማሪም በምሥራቃዊ ትግራይ ሀገረ ስብከት በማቅናት አጽቢ ወምበርታ ወረዳ በደብረ ቅዱሳን ዲቦ ቅድስት ማርያም አንድነት ገዳም ማኅበሩ በብር 225,343.65 /ሁለት መቶ ሃያ አምስት ሺህ ሦስት መቶ አርባ ሦስት ብር ከ65 ሣንቲም/ ተግባራዊ ያደረገውን የሽመና ውጤቶችን መሥሪያ አዳራሽ ሠርቶ በማጠናቀቅ፤ የሽመና ቁሳቁስ በማሟላት፤ እንዲሁም የልብስ ሥፌት መኪናዎችን ገዝቶ በማቅረብ ርክክብ ተደርጓል፡፡
የደቡብ ኦሞ ሀገረ ስብከት ከማኅበረ ቅዱሳን ጋር በመተባበር ከ2004- 2007 ዓ.ም. 16,630 አዳዲስ አማንያንን በማስተማር መጠመቃቸውን የሀገረ ስብከቱ ሥራ አስኪያጅ አስታወቁ፡፡
የጂንካ ደብረ ቀራንዮ መድኀኔዓለም ቤተ ክርስቲያን ሕንፃ አሠሪ ኮሚቴ ሰብሳቢ አቶ ጀማል ዑመር /ዐምደ ሚካኤል/ ባቀረቡት ሪፖርት የቤተ ክርስቲያኑ ሕንፃ ሥራ በፍጥነት እንዲጠናቀቅ እገዛ ላደረጉ ሁሉ ምስጋናቸውን ያቀረቡ ሲሆን፤ የቤተ ክርስቲያኑን ዲዛይን በተመለከተም ሲገልጹ “የወንጌል አርበኞች የሆኑት የማኅበረ ቅዱሳን ጂንካ ማእከል አባላት የቤተ ክርስቲያኑን ዲዛይን በነጻ በመሥራት እገዛ አድርገዋል” ብለዋል፡፡
በሰሜን ጎንደር ሀገረ ስብከት በደምቢያ ወረዳ በጣና ሐይቅ ውስጥ በ1335 ዓ.ም. ተገድማ የነበረችው የጀበራ ማርያም አንድነት ገዳም ከፈረሰች ከበርካታ ዘመናት በኋላ ዳግም ለማቋቋም ከፍተኛ ጥረት እየተደረገ መሆኑን ገዳሙን መልሶ ለማቋቋም በማስተባበር ላይ የሚገኙት አባ ዘወንጌል ገለጹ፡፡
በስድስት ወራት ውስጥ የተጀመረው ግንባታም በመፋጠን ላይ ሲሆን፤ ሠርቶ ለማጠናቀቅም በርካታ ሥራዎች ይቀራሉ፡፡ የጣሪያ ቆርቆሮ፤ የበር፤ የመስኮት፤ የቤተ መቅደስ፤ የማጠናቀቂያ ሥራዎችና ሌሎችም ስለሚቀሩት በባለሙያዎች ተጠንቶ 1.2 ሚሊዮን ብር ድጋፍ እንደሚያስፈልገውና ይህንን ለማሟላት የሕንፃ አሠሪ ኮሚቴው በችግር ውስጥ እንደሚገኝ አባ ዘወንጌል ገልጸዋል፡፡ በጎ አድራጊ ምእመናንም ገዳሟ ያለችበትን ሁኔታ በመረዳት ድጋፍ እንዲያደርጉ ጥሪያቸውን አስተላልፈዋል፡፡


ከአጸደ ሥጋ ዓለም በሞት ተለይተው በአጸደ ነፍስ የሚገኙ ቅዱሳን ፓትርያኮችና ብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳት፤ ጥቅምት 9 ቀን 2007 ዓ.ም በመንበረ ፀባዖት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል ጸሎተ ፍትሐት ተደረገላቸው፡፡ ሥርዓተ ጸሎተ ፍትሐቱ በተለይ ለብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ባስልዮስ፣ ለብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ቴዎፍሎስ፣ ለብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ተክለ ሃይማኖትና ለብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ጳውሎስ፣ ብጹዓን ሊቃነ ጳጳሳትን እንዲሁም ቤተክርስቲያንን አገልግለው ያለፉ አበው የታሰቡበትና በረከታቸው በአጸደ ሥጋ ላለነው እንዲደርስ ጸሎት የተደረገበት ነው፡፡
ቅዱስነታቸው አያይዘውም “እናትና አባትህን አክብር የሚለውን የጌታን ትእዛዝ ለመፈጸም በዚህ ቦታ ተገኝተናል በመንፈስ ወልደውና በምግባር አሳድገው ለዚህ ስላበቁን እነሱን ማክበርና ማስታወስ ግዴታችን ነው፡፡ ስለሆነም ይህ መታሰቢያ በዓል በየዓመቱ እንዲከበር በቅዱስ ሲኖዶስ መወሰኑ የሚመሰገን ነው፡፡” በማለት ቀደምት የቤተክርስቲያን አበውን መዘከር እንደሚገባ አሳስበዋል፡፡
በዚሁ እለት የብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ጳውሎስ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት፣ የዓለም አብያተ ክርስቲያናት ምክር ቤት ፕሬዝዳንት የመታሰቢያ ሐውልት ተመርቋል፡፡ የመታሰቢያ ሐውልቱ የተሠራው በቅዱስ ሲኖዶስ መመሪያና ትዕዛዝ ሲሆን፤ ወጭውን ደግሞ ጠቅላይ ቤተ ክህነት መሸፈኑን የጠቅላይ ቤተ ክህነት ዋና ሥራ አስኪያጁና የወላይታ ኮንታና ዳውሮ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ ማቴዎስ አስታውቀዋል፡፡ 
የ33ኛው ሰበካ መንፈሳዊ ጉባኤ ማጠቃለያ መርሐ ግብር የተጀመረው ከረፋዱ 2፡46 ነበር፡፡ ብፁዕ ወቅዱስ ፖትርያርክ አቡነ ማትያስ ጉባኤውን በጸሎት ከከፈቱ በኋላ ብፁዕ ዶ/ር አቡነ ገብርኤል “ወነአምን በአሐቲ ቅድስት ቤተ ክርስቲያን” በሚል ርዕስ ከምንጊዜውም በላይ የቤተ ክርስቲያንን
በመቀጠልም ብፁዕ አቡነ ማቴዎስ የጠቅላይ ቤተ ክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ ለሦስት ቀናት በቀረቡት ሪፖርቶች ላይ ውይይት እንዲደረግ ጋብዘዋል፡፡ ሆኖም ግን ቅዱስ ፓትርያርኩ በጉባኤው መክፈቻ ዕለት ማኅበረ ቅዱሳንን አስመልክተው በሰጡት መግለጫ ላይ ብቻ ሰፊና ጠንካራ ውይይቶች ተደርጓል፡፡
በመጨረሻም በበጀት ዓመቱ በልማት፣ ዓመታዊ ገቢ