‹‹የምሥራች እነግራችኋለውና አትፍሩ›› (ሉቃ.፪፥፲)

ውድ የእግዚአብሔር ልጆች እንዴት አላችሁ? እንኳን አደረሳችሁ! የልደት በዓል ዝግጅት እንዴት ነው? ልጆች ትምህርተስ እየበረታችሁ ነውን? አሁን የዓመቱ አጋማሽ የፈተና ወቅት በመሆኑ መምህራን ሲያስተምሩን ከመጻሕፍት ስናነብ የነበሩትን ምን ያህሉን እንደተረዳን የምንመዘንበት ጊዜ ነው! መቼም በርተታችሁ ስታጠኑና ያልገባችሁን ስትጠይቁ ስለ ነበር በፈተና የሚቀርቡላችሁን ጥያቄዎች በትክክል እንደምትመልሱ ተስፋችን እሙን ነውና በርቱ! ያለንበት ጊዜ ደግሞ የበዓላት ወቅት ስለሆነ በዚህ እንዳትዘናጉ፣ ከሁሉ ቅድሚያ ትኩረት ለትምህርት መስጠት አለባችሁ።፡ ነገ አገር ተረካቢዎችና ታሪክን ጠባቂዎች ስለምትሆኑ በርቱና ተማሩ!

ታዲያ ልጆች ዕውቀት ማለት በተግባር መተርጎም መሆኑን እንዳትዘነጉ! አንድ ሰው ተማረ፤ አወቀ ማለት ክፉ ነገር ከማድረግ ተቆጠበ፤ ሰዎችን ረዳ (ደገፈ)፤ ለሰዎች መልካም ነገርን አደረገ፤ ሌላውን ወደደ ማለት ነው፤ መማራችሁ ለዚህ መሆን አለበት፡፡ ቅን፣ ደግ፣ አስተዋይ እንዲሁም ወገኑን የሚወድ ሰዎች ሆናችሁ ለመኖር ሁል ጊዜ መበርታት አለባችሁ:: መልካም ልጆች! ዛሬ ስለ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ልደት እንማራለን!

‹‹የእግዚአብሔር መልአክ በሚፈሩት ሰዎች ዙሪያ ይሰፍራል፤ ያድናቸውማል›› (መዝ.፴፫፥፯)

ውድ የእግዚአብሔር ልጆች! ለከበረው ጤንነታችሁ እንዴት አላችሁልን? ትምህርት እንዴት ነው? ደጋግመን ስለ ትምህርታችሁ የምንጠይቃችሁ በዚህ ጊዜ የእናንተ ተቀዳሚ ተግባራችሁ መሆን ያለበት እርሱ ስለሆነ ነው፡፡ መማርና ማወቅ ብልህና አስተዋይ ያደርጋል፤ ታዲያ ስትማሩም ለማወቅ እና መልካም ሰው ለመሆን መሆን አለበት! ደግሞም የዓመቱ አጋማሽ ፈተናም እየደረሰ በመሆኑ በርትታችሁ ማጥናታችሁ መምህራን የሚያወጡትን ጥያቄ ለመመለስ ብቻ መሆን የለበትም፡፡ ጥያቄውን ከመመለስ በተጨማሪ ምን ያህል እውቀት እንዳገኛሁ ልታውቁበት ይገባል!

ውድ የእግዚአብሔር ልጆች! ለዛሬ የምንነግራችሁ ታሪክ በታኅሣሥ ፲፱ ቀን ዓመታዊ ክብረ በዓሉ ስለሚከበርለት ቅዱስ ገብርኤልና ስላዳናቸው ሦስቱ ሕፃናት ነው፡፡

‹‹አትስረቅ›› (ዘፀ.፳፥፲፭)

ውድ የእግዚአብሔር ልጆች! እንዴት አላችሁ? ትምህርት እንዴት ነው? እየበረታችሁ ነውን? የመንፈቀ ዓመቱ (የዓመቱ ግማሽ) የትምህርተ ዘመን ሊጠናቀቅ የቀሩት ጥቂት ሳምንታት ናቸው፡፡ ለመሆኑ ምን ያህል ዕውቀት አገኛችሁ? ትናንት የማታውቁት አሁን አዲስ የተጨመረላችሁ ዕውቀት ምንድን ነው? ይህን ራሳችሁን መጠየቅ አለባችሁ? መማራችሁ ከክፍል ወደ ክፍል ለመሸጋገር ብቻ ሳይሆን ባላችሁ ግንዛቤ ላይ ሌላ ዕውቀት ለመጨመር ነውና በርቱ! መማራችሁ ለተሻለ ሕይወት፣ ዛሬን ከትላንትና፣ ነገን ደግሞ ከዛሬ የተሻለ ሆኖ እንድታገኙት ሊሆን ይገባል፡፡ መልካም! ለዛሬ የምንማረው ከዐሥርቱ ትእዛዛት መካከል አንድ ስለሆነው ‹‹አትስረቅ›› ስለሚለው የእግዚአብሔር ሕግ ነው!

‹‹ስለምጽፍላችሁ ነገር እነሆ በእግዚአብሔር ፊት ሐሰት አልናገርም›› (ገላ.፩፥፳)

ውድ የእግዚአብሔር ልጆች! እንዴት አላችሁ? ትምህርት እንዴት ነው? እየበረታችሁ ነውን? መምህራን የሚነግሯችሁን በትኩረት በማዳመጥ፣ መጻሕፍትን በማንበብና ያልገባችሁን በመጠየቅ ትላንት ከነበራችሁ ግንዛቤ የተሻለ ዕውቀትን እየቀሰማችሁ እንደሆነ ተስፋ እናደርጋለን! መልካም!

ውድ የእግአብሔር ልጆች! ባለፉት ጊዜያት በዓላትን አስመልክተን የቅዱሳንን ታሪክ አዘጋጅተን ባቀረብንላችሁ መሠረት ከቅዱሳን የሕይወት ታሪክ በርካታ ቁም ነገሮችን ስንማማር እንደነበር ታስታውሳላችሁ አይደል? በተለይ ሥርዓትን አክብረን መኖረ እንደሚገባን፣ በቤተ እግዚአብሔር  መኖር ደግሞ ታላቅ በረከትን እንደሚያስገኝልን፣ ለቅዱሳን ስለተሰጣቸው ክብርና የቅድስና ሕይወታቸው ምን እንደሚመስል ተመልክተናል፡፡ ለዛሬ ደግሞ ያዘጋጀንላችሁ እጅግ ጠቃሚ የሆነ ትምህርት ሲሆን ሐሰት መናገር እንደማይገባ እንዲሁም እውነተኛና ታማኝ መሆን እንዳለብን ልናስተምራችሁ ወደድን፤  በጥሞና ተከታተሉን!

ሊቀ ዲያቆናትና ቀዳሜ ሰማዕት ቅዱስ እስጢፋኖስ

ውድ የእግዚአብሔር ልጆች እንዴት አላችሁልን? ትምህርት እንዴት ነው? መቼም በክረምቱ የዕረፍት ጊዜያችሁ ትምህርት እስኪከፈት በጣም ጓጉታችሁ እንደነበር እናስባለን! ይኸው ተከፈተላችሁ! እንግዲህ በርትታችሁ ከአሁኑ መማር፣ ማጥናት፣ የቤት ሥራን መሥራት፣ ያልገባችሁን መጠየቅ ይገባችኋል፡፡ ገና ነው እያላችሁ እንዳትዘናጉ ጥናቱን አሁኑኑ ጀምሩ! የጨዋታም ሆነ ቴሌቪዥን የምታዩበት ጊዜ ከትምህርታችሁ ጋር በማይጋጭ መልኩ መሆን አለበት፡፡ ከሁሉም ትምህርታችሁን አስቀድሙ! ውድ እግዚአብሔር ልጆች! ለዛሬ ያዘጋጀንላችሁ የሊቀ ዲያቆናትና የቀዳሜ ሰማዕት ቅዱስ እስጢፋኖስን ታሪክ ነው፡፡

ቅድስት አርሴማ

ውድ የእግዚአብሔር ልጆች! ለከበረው ጤንነታችሁ እንዴት አላችሁ! የክረምት ወቅት አልፎ አዲሱን ዓመት ተቀብለናልና ለዚህ ያደረሰንን ፈጣሪያችንን ማመስገን ይገባል! ልጆች! መስቀል በዓል እንዴት ነበር? በሰላም በፍቅር አከበራችሁ አይደል? የእኛን ምክርም ተቀብላችሁ ለመጪው የትምህርት ዘመን ዝግጅት ስታደርጉ እንደቆያችሁ ደግሞ ተስፋችን ነው፡፡ አሁን ደግሞ ትምህርት ስለጀመራችሁ በርትታችሁ መማርን እንዳትዘንጉ! ከአሁኑ ጀምራችሁ መምህራን የሚነግሯችሁን በንቃት ተከታተሉ፤ መጻሕፍትን አንብቡ፤ ያልገባችሁን ጠይቁ፤ የቤት ሥራችሁን በአግባቡ ሥሩ፤ የጨዋታ ጊዜያችሁንና ቴሌቪዥን የምታዩበትን ጊዜ መቀነስ አለባችሁ፤ አሁን የእናንተ ተግባር፣ እይታ፣ ሥራ፣ ጉዳይ ሁሉ ትምህርት እና ትምህርት ብቻ ስለሆነ ጎበዝ ተማሪዎች ሁኑ፤ መልካም!

ውድ የእግዚአብሔር ልጆች! ለዛሬ ያዘጋጀንላችሁ ታሪክ የቅድስት አርሴማን ነው፤

ቅዱስ መስቀል

ውድ የእግዚአብሔር ልጆች! እንዴት አላችሁ? እንኳን ከዘመነ ማርቆስ ወደ ዘመነ ሉቃስ አሸጋግሮ በሰላም ለዚህ ዕለት አደረሳችሁ! ዕንቁጣጣሽ እንዴት አለፈ? መቼም ደስ ብሏችሁ እንዳሳለፋችሁ ተስፋችን እሙን ነው፡።  መልካም! የአዲስ ዓመት ትምህርት ለመጀመር እንዴት እየተዘጋጃችሁ ነው? ባለፈው ዓመት በትምህርታችን ደከም ያለ ውጤት አስመዝግበን የነበርን ዘንድሮ በርትተን በመማር በጥሩ ውጤት ከክፍል ክፍል ለመሻገር ከአሁኑ ማቀድና መበርታት አለብን፡፡ እንዲሁም ደግሞ ለአገርና ለቤተ ክርስቲያን እየጸለይን የሰላምን ዘመን ተስፋ እናድርግ! መልካም!

ውድ የእግዚአብሔር ልጆች! ባለፉት ጊዜያት ለእናንተ ያስተምራሉ በማለት በጻፍንላችሁ በርካታ ቁም ነገሮችን ስንማማር እንደነበር ታስታውሳላችሁ አይደል? አሁን ደግሞ ስለ ቅዱስ መስቀሉ በዓል ጥቂት ልናካፍላችሁ ወደድን፤ መልካም ቆይታ!

ቅድስት ክርስቶስ ሠምራ

ውድ የእግዚአብሔር ልጆች!  ለከበረው ጤንነታችሁ እንዴት አላችሁ? የጾመ ፍልስታ ወቅት እንዴት ነበር? እንኳን አደረሳችሁ!  የክረምት ወቅት አልፎ አዲሱን ዓመት ልንቀበል ቀናት ብቻ ቀርተውናል! እህቶቻችንን ለዚህ ያደረሰንን ፈጣሪ በዝማሬ ያመሰግናሉ፤ ልጆች! ለመሆኑ አበባ አየሽ ወይ? እያልን የምንዘምረው “የተዘራው ዘር በቅሎ ቅጠል ከዚያም ደግሞ አበባን ሰጥቷል፤ ቀጥሎ ደግሞ ፍሬን ይሰጣል” በማለት የምሥራችን እያበሠሩ ለዚህ ያደለንን ፈጣሪ ያመሰግናሉ፡፡ ልጆች! ሌላው ደግሞ መዘንጋት የሌለባችሁ ነገር ለመጪው የትምህርት ዘመን ዝግጅት ማድረግ እንዳለባችሁ ነው፤ መልካም!
ውድ የእግዚአብሔር ልጆች! ለዛሬ ያዘጋጀንላችሁ ታሪክ የቅድስት ክርስቶስ ሠምራን ነው፤

ትዕግሥተኛዋ እናት ቅድስት እንባመሪና

ውድ የእግዚአብሔር ልጆች!  ለከበረው ጤንነታችሁ እንዴት አላችሁ? የጾምን ወቅት እንዴት እያሳለፋችሁት ነው? አባቶቻችን ሊቃውንት ስለ ጾም እንዲህ ይላሉ፤ ጾም ማለት ከምግብና ከውኃ መከልከል ብቻ ሳይሆን ከክፉ ሥራም መታቀብ (መከልከል) ነው፤ ጾም የጽድቅ በር ናት፣ ጾም ለመልካም ነገር የምታነሣሣን ናት፤ ውድ እግዚአብሔር ልጆች! ስንጾም ከጸሎትና  ከስግደት ጋር፣ ቤተ ክርስቲያን በመሄድ በማስቀደስ ፣ታዛዦች በመሆን የጾሙን ጊዜ ልናሳልፍ ይገባል፡፡ መልካም!

ውድ እግዚአብሔር ልጆች! ለዛሬ ያዘጋጀንላችሁ ታሪክ የቅድስት እንባመሪናን ነው፡፡

ቅድስት መስቀል ክብራ

ውድ የእግዚአብሔር ልጆች! እንዴት አላችሁልን? ወርኃ ክረምቱ እንዴት ነው? መቼም ዝናቡና ቅዝቃዜው እንደፈለግን እንዳንጫወት አድርጎናልና ከቦታ ቦታ ለመንቀሳቀስም አያመችም፡፡ አብዛኛውን ጊዜ ቤት ውስጥ እንደምንቆይ ይታወቃል፡፡ ታዲያ ውድ የእግዚአብሔር ልጆች! ይህንን አጋጣሚ በመጠቀም መጻሕፍትን ማንበብ፣ ለቀጣዩ ዓመት የትምህርት ጊዜ የሚረዱንን ጥናቶች በማድረግ ልንዘጋጅ ያስፈልጋል፤ ጊዜያችንን በአግባቡ በቁም ነገር ላይ ማዋል አለብን! ደግሞም በጉጉት የምንጠብቃት ጾመ ፍልሰታም እየደረሰች ነው!

ውድ የእግዚአብሔር ልጆች! ለዛሬ ያዘጋጀንላችሁ የቅድስት መስቀል ክብራን ታሪክ ነው፡፡