‹‹ለተቀበሉት ሁሉ ግን÷ በስሙ ለሚያምኑት ለእነርሱ የእግዚአብሔር ልጆች ይሆኑ ዘንድ ሥልጣንን ሰጣቸው›› (ዮሐ. ፩፥፲፪)
የክርስቶስ አካል እንደመሆናችን መጠን ደግሞ ይህን ኃላፊነት በተለያየ መልኩ በሕይወታችን ልንተገብር እንደሚገባ መረዳት ያስፈልጋል፡፡ ክርስቲያኖች ከአምላካቸው የተቀበሉትን ትእዛዝ መፈጸምም አለባቸው፡፡ ወላጆች ልጆቻቸውን በልጅነት ጥምቀት በማስጠመቅ፣ በቤተ ክርስቲያን ሥርዓት በማሳደግ እና ሥርዓተ አምልኮቱን እንዲፈጽሙ በመርዳት ማሳደግ አለባቸው፡፡ ይህንንም መጀመር ያለባቸው ልጆቹ ሰባት ዓመት ሲሞላቸው እንደሆነ የቤተ ክርስቲያን አስተምህሮ ላይ ተጠቅሷል፡፡