ሥርዓተ አምልኮ
በጸሎትና በስግደት እንዲሁም በምጽዋት የታገዘ ጾም በእግዚአብሔር ፊት የተወደደ በመሆኑ ድኅነትን ማሰጠት ብቻም ሳይሆን በረከትን ያስገኛል፡፡ በዚህም የተነሣ ሥራችን፣ ትዳራችን እንዲሁም አገልግሎታችን ይባረክልናል፡፡
በጸሎትና በስግደት እንዲሁም በምጽዋት የታገዘ ጾም በእግዚአብሔር ፊት የተወደደ በመሆኑ ድኅነትን ማሰጠት ብቻም ሳይሆን በረከትን ያስገኛል፡፡ በዚህም የተነሣ ሥራችን፣ ትዳራችን እንዲሁም አገልግሎታችን ይባረክልናል፡፡
ቅዱስ ዳዊት “ኢትዝክር ለነ አበሳነ ዘትካት ፍጡነ ይርከበነ ሣህልከ እግዚኦ እስመ ተመንደብነ ፈድፋደ፤ የቀደመውን በደላችንን አታስብብን፥ ምሕረትህ በቶሎ ታግኘን፥ እጅግ ተቸግረናልና” እንዳለ የቀደመ በደላችንን ሳያስብብን ጭንቀታችንን ችግራችንን ይቅር ብሎ ወደ እዚህ ምድር መጥቶ የምሥራች፣ ብርሃን፣ መንገድ፣ መስታወት፣ የሕይወት ዛፍ የሆነችውን ወንጌልን ሰበከን፤ አስተማረን። (መዝ.፸፰፥፰) ሐዋርያትንም “ሑሩ ውሰተ ኩሉ ዓለም ወስብኩ ወንጌለ ለኩሉ ፍጥረት፤ ወደ ዓለም ሁሉ ሂዱ፤ ወንጌልንም ለፍጥረት ሁሉ ስበኩ” በማለት በይሁዳ፣ በኢየሩሳሌም፣ በሰማርያና እስከ ዓለም ዳርቻ እንዲያስተምሩ ላካቸው። (ማር.፲፮፥፲፭)
በሕይወታችን ለሚገጥመን ማንኛውም ችግር ከእግዚአብሔር ዘንድ መፍትሔ ይኖረዋል፡፡ በእርሱ አምነንና ታምነን እስከኖርን ድረስ ከመከራና ከሥቃይ ያወጣናል፡፡ ሰዎች በተለያዩ ጊዜያት በሕይወታቸው ውስጥ ችግር ሊገጥማቸው ይችላል፡፡ የሚረዳቸው ቤተሰብም ሆነ ዘመድ ከሌላቸው ደግሞ ችግራቸውን ስለሚያባብሰው ወደከፋ መከራ ውስጥ ሲገቡ ሰምተንም ሆነ ተመልክተን ይሆናል፡፡ ነገር ግን አምላካችን እግዚአብሔር ሰውን የሚፈትነው ለበጎ እንደሆነ በማወቅና በመረዳት የነገን ተስፋ አድርጎ መኖር ይኖርብናል እንጂ ተስፋ መቁርጥ ወይም ማማረር አይገባም፡፡ በተቻለው መጠን ለኑሯችን ተሯሩጠን የዕለት ጉርሻችን መሙላት እንዲሁም ወደ ተሻለ ሕይወት መትጋት ይገባል፡፡
‹‹የፀሐይን፣ የጨረቃን፣ የከዋክብትን ሥራቸውን ዕወቅ፤ ከሁሉ የሚደንቅ ክበባቸውን ከሁሉ የሚበልጥ ብርሃናቸውን ሁሉ ዕወቅ፤ በየወገናቸው የሚያበሩ የሚመላለሱ የእነዚህን የምሳሌያቸውን ሥራ ዕወቅ፤ ሁሉ ጊዜ እርስ በእርሳቸው እንደምንም እንደሚቀራረቡ ዳግመኛም እንደምንም እንደሚራራቁ ዕወቅ…›› (ሃይማኖተ አበው ዘቅዱስ ባስልዮስ ምዕራፍ ፴፭፥፲፯)
ዕለተ ማክሰኞ የፍጥረት ሦስተኛ የምስጋና ሁለተኛ ቀን ነች፤ በባሕረ ሐሳብ ቀመር ደግሞ ዕለተ ቀመር ትባላለች፤ በፀሐይ አቆጣጠር ሰባተኛ ቀን ትባላለች፡፡ ዛሬ ግን የምናነሣው በዕለተ ፍጥረት ስለተከናወነባት ክንዋኔ ነው፡፡
እግዚአብሔር ያለ ምክንያት የፈጠረው ፍጥረት የለምና ነፋስንም በምክንያት ፈጥሮታል፡፡ ልበ አምላክ ክቡር ዳዊት በመዝሙሩ “ሰማያት የእግዚአብሔርን ክብር ይናገራሉ፤ የሰማይም ጠፈር የእጁን ሥራ ያወራል፡፡ ቀን ለቀን ነገርን ታወጣለች፤ ሌሊትም ለሌሊት እውቀትን ትናገራለች” በማለት እንደዘመረው ሥነ ፍጥረት አእምሮ ላለው የሰው ልጅ የእግዚአብሔርን ባሕርያዊ መገለጫዎች ሥራና ፈቃዳት ያስተምራሉ፡፡ (መዝ.፲፰፥፩) ሰውንም ሲፈጥረው ከዐራቱ ባሕርያተ ሥጋ አምስተኛ ባሕርየ ነፍስን አድርጎ በመልኩና በምሳሌው እንደፈጠረው የታወቀ ነው፡፡ (ዘፍ. ፩፥፳፮) እነዚህ አራቱ ባሕርያተ ሥጋ የሚባሉትም ነፋስ፣ እሳት፣ መሬትና ውኃ ናቸው፡፡ በሥነ ፍጥረት ትምህርት እግዚአብሔር ሰውን ከእነዚህ ዐራት ባሕርያት የፈጠረበት ምክንያት በምልዓትና በስፋት ይተነተናል፡፡ በዚህ አጠር ያለ ጽሑፋችንም ከነፋስ ምን እንማራለን? የሚለውን እናነሣለን፡፡
ታላቁ የቤተ ክርስቲያናችን አባት ሊቀ መዘምራን ዕቁበ ጊዮርጊስ ሲናገሩ “እግዚአብሔር ኃያል ነኝ ሲል እሳትን ፈጠረ“ ይላሉ፡፡
እግዚአብሔር በዕለተ ሰኑይ በቀዳሚት ሰዓት ሌሊት ‹‹ጠፈር ይሁን፤ ውኃም ከውኃ ይለይ›› ብሎ ቢያዘው ከዚህ እስከ ብሩህ ሰማይ ሞልቶ የነበረውን ውኃ ከአራት ከፍሎ አንድን እጅ በመካከል ከምሥራቅ እስከ ምዕራብ ከሰሜን እስከ ደቡብ ዘረጋው፡፡ (ዘፍ.፩፥፮) እንደ ቤተ መንግሥት አዳራሽ ወደ ላይ ጠበብ አድርጎ እንደ ብረት አጸናው፤ ይህ የምናየው ሰማይ ነው፤ ጠፈር ይባላል፡፡ ጠፈር ማለትም ሥዕለ ማይ (የውኃ ሥዕል) ማለት ነው፡፡ እግዚአብሔር ጠፈርን መፍጠሩ ስለምንድነው? ቢሉ ረቡዕ የሚፈጥረውን ፀሐይን ሊያቀዘቅዝ ሰውም ይህን እያየ ሰማያዊ ርስት እንዳለው እንዲያውቅ ነው፡፡ እጅግም ነጭ ከሆነ ዓይን እየበዘበዘ እያንጸባረቀ ለሰው የደዌ ምክንያት ይሆን ነበርና፡፡ በድስት ያለ ውኃ በሚታጠብ ጊዜ የእሳት ማቃጠል ሲበዛበት እንደሚሰበር ጠፈርም የፀሐይ ማቃጠል ሲበዛበት እንደ ሸክላው በፈረሰ ነበርና እንዲያጸናው ሐኖስን በላይ አደረገለት፡፡ (መጸሐፈ ሥነ ፍጥረት ገጽ ፳-፳፫
በሥነ ፍጥረት መጀመሪያ ቀን ‹‹ብርሃን ይሁን›› በማለት የተናገረው አምላካችን ልዑል እግዚአብሔር ነው፡፡ (ዘፍ.፩፥፫) ‹‹ብርሃን ይሁን›› በማለት በተናገረ ጊዜም ጨለማ ተገፈፈ፡፡ መጽሐፈ ሥነ ፍጥረት እንደሚነግረን ቅዱሳን መላእክትም ይህ ብርሃን ዕውቀት ሆኗቸው አምላካቸው እግዚአብሔርን ‹‹ቅዱስ ቅዱስ ቅዱስ›› በማለት በአዲስ ምስጋና አመሰገኑት፡፡ ‹‹እኔ ፈጣሪያችሁ ነኝ›› ያለ የሰይጣን ክህደትም በብርሃኑ ተጋለጠ፡፡ (ሊቀ መዘምራን ሞገስ ዕቁበ ጊዮርጊስ መጽሐፈ ሥነ ፍጥረት)
ውኃ ከምንጭ ተገኝቶ እየፈሰሰ የፍጥረትን ጥማት ያረካል፡፡ በውኃ ሰው ሕይወቱን ያለመልማል፤ እንስሳትና አራዊትም እንዲሁ፡፡ ዕፅዋትና አዝርዕትም ያለ ውኃ አይለመልሙም፤ አይበቅሉምም፡፡ በቅዱሳት መጻሕፍት እንደ የአገባቡ መምህራን በውኃ ምንጭ ተመስለዋል፡፡ ከምንጭ ንጹሕ ውኃ ተገኝቶ ፍጥረትን እንደሚያረሰርስ ከመምህራንም አንደበት በውኃ የሚመስል ቃለ እግዚአብሔር እየፈሰሰ የሰው ልጆችን በጽድቅ እንዲኖኑ ያደርጋል፡፡ ምእመናን ውኃ ቃለ እግዚአብሔር ከሚገኝባቸው እውነተኞች መምህራን እግር ሥር ተገኝቶ በመማር ከድርቀት ኃጢአት ወደ ልምላሜ ጽድቅ ይመጣሉ፤ የመንፈስ ፍሬንም ያፈራሉ፡፡