Entries by Mahibere Kidusan

የለንደን ደ/ጽዮን ቅድስት ማርያም ቤተ ክርስቲያን እንደገና ተከፍታ አገልግሎት መስጠት ጀመረች

 ታኅሣሥ 25 ቀን 2006 ዓ.ም. 

 

ከUK ቀጠና ማዕከል

uk maceleየኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ካህናትን እና ምእመናንን ባሳዘነ ሁኔታ ከዘጠኝ ወራት በላይ ተዘግታ የቆየችው የለንደን ርእሰ አድባራት ደብረ ጽዮን ቅድስት ማርያም ቤተ ክርስቲያን እሁድ ታኅሣስ ፳ ቀን ፳፻፮ ዓ.ም. የሰሜን ምዕራብ አውሮፓ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ብጹዕ አቡነ እንጦንስ በተገኙበት በይፋ እንደገና ተከፍታ አገልግሎት መስጠት ጀመረች።

ማኅበረ ቅዱሳን የአልባሳት ማሰባሰቢያ መርሐ ግብር አዘጋጀ

ታኅሣሥ 18 ቀን 2006 ዓ.ም.

በታመነ ተ/ዮሐንስ

tena gedamateበኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ማኅበረ ቅዱሳን ‹‹የአብነት መምህራንና ተማሪዎችን ጤና ለመጠበቅ›› በሚል ከታኅሣሥ 1 እስከ ጥር 6 ቀን 2006 ዓ.ም ድረስ የሚቆይ መርሐ ግብር አዘጋጀ፡፡

ያመኑትም ሕዝብ አንድ ልብ አንዲትም ነፍስ ነበሩአቸው

ትኅሣሥ 17 ቀን 2006 ዓ.ም.

በእንዳለ ደምስስ

tsreha tsion 2በማኅበረ ቅዱሳን የኅትመትና ኤሌክትሮኒክስ ሚዲያ ክፍል መደበኛና ኢ-መደበኛ አባላት በአገልግሎት ዙሪያ ለመወያየትና ከጽርሐ ጽዮን ዘተዋሕዶ የአንድነት ኑሮ ማኅበር አባላት ጋር የልምድ ልውውጥ ለማድረግ እንዲቻል ከአዲስ አበባ በምዕራብ አቅጣጫ ቡራዩ አካባቢ ወደሚገኘው ጽርሐ ጽዮን ዘተዋሕዶ የአንድነት ኑሮ ማኅበር መንደር ታኅሣሥ 12 ቀን 2006 ዓ.ም. የጉዞ መርሐ ግብር አካሒዷል፡፡

አባላቱ አንድ የማኅበረ ቅዱሳን አገልጋይ በተከራየላቸው መለስተኛ አውቶብስ (ሃይገር ባስ) በመሳፈር ከ45 ደቂቃ ጉዞ በኋላ ከረፋዱ 5፡00 ሰዓት ላይ የጽርሐ ጽዮን ዘተዋሕዶ የአንድነት ኑሮ ማኅበር ደረስን፡፡ በማኅበሩ አባላት በመሠራት ላይ የሚገኘውን የጽርሐ ጽዮን ዘተዋሕዶ አቡነ ተክለ ሃይማኖት ቤተ ክርስቲያን እየተሳለምንና በነፋሻማው አየር እየታገዝን ወደ ውስጥ ዘለቅን፡፡ ግቢው በተለያዩ አጸዶች ተውቧል፡፡ ነፍስ ምግቧን ታገኝ ዘንድ ትክክለኛው ሥፍራ በመሆኑ የነፍሳችንን ረሃብ ለማስታገሥ ቸኩለናል፡፡ የአባቶችን ቡራኬ ተቀብለን አጭር የግል ጸሎታችንን አድርሰን ለጉብኝቱ ተዘጋጀን፡፡ ጉብኝቱ የተጀመረው ስለ ጽርሐ ጽዮን ዘተዋሕዶ የአንድነት ኑሮ ማኅበር አመሠራረት ዲያቆን ደቅስዮስ ገለጻ በማድረግ ነበር፡፡

ግብረ ፊልጶስ ሲምፖዚየም ተካሄደ

 ታኅሣሥ 16 ቀን 2006 ዓ.ም.

በእንዳለ ደምስስ

በማኅበረ ቅዱሳን የትምህርትና ሐዋርያዊ አገልግሎት ዋና ክፍል የስብከተ ወንጌል ማስፋፊያ መርሐ ግብር “ግብረ ፊልጶስ” የተሰኘ ሲምፖዚየም ታኅሣሥ 12 እና 13 ቀን 2006 ዓ.ም. በቅድስት ሥላሴ መንፈሳዊ ኮሌጅ ግቢ ውስጥ አካሄደ፡፡

gebra felp 1ታኅሣሥ 12 በብፁዕ አባታችን አቡነ ማትያስ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የካናዳና አካባቢው ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ በጸሎት የተከፈተ ሲሆን፤ በመርሐ ግብሩ ላይ ከተለያዩ የኢትዮጵያ ጠረፋማ አካባቢዎች ከደቡብ ኦሞና ከቤንሻንጉል ጉሙዝ ወረዳዎች ተጋብዘው የመጡ ከዚህ በፊት በሀገረ ስብከቱና በማኅበረ ቅዱሳን ትምህርትና ሐዋርያዊ አገልግሎት የስብከተ ወንጌል ማስፋፊያ በጋራ ተምረውና ተጠምቀው የነበሩ አገልጋዮችና ምእመናን ተገኝተዋል፡፡

የሐዊረ ሕይወት መርሐ ግብር ደብረ መድኀኒት ኢየሱስ ክርስቶስ ቤተ ክርስቲያን

 ታኅሣሥ 9 ቀን 2006 ዓ.ም.

በእንዳለ ደምስስ

ሪፖርታዥ፡-

hawi 01ማኅበረ ቅዱሳን ለአምስተኛ ጊዜ ያዘጋጀው የሐዊረ ሕይወት መርሐ ግብር በደብረ ዘይት ከተማ ደብረ መድኀኒት ኢየሱስ ክርስቶስ ቤተ ክርስቲያን ታኅሣሥ 6 ቀን 2006 ዓ.ም. ከ6000 በላይ ምእመናን በተገኙበት በድምቀት አካሔደ፡፡

ከዋዜማው ጀምሮ መርሐ ግብሩን የተሳካ ለማድረግ የማኅበሩ ሐዊረ ሕይወት አዘጋጅ ኮሚቴ በሚመድበው መሠረት የየክፍሉ አገልጋዮች በአገልግሎት ተጠምደዋል፡፡ መርሐ ግብሩን የተሳካ ለማድረግ ሁሉም ይጣደፋል፤ የጎደለውን ይሞላል. . . ፡፡

ከሌሊቱ 12፡00 ጀምሮ አምስት ኪሎ ቅድስት ማርያም ቤተ ክርስቲያን አጠገብ ከሚገኘው ከማኅበረ ቅዱሳን ሕንፃ ጀምሮ በተለምዶ ሰባ ደረጃ እስከሚባለው ሠፈር ድረስ ሰባ 1ኛ ደረጃ የሚሆኑ የከፍተኛ አገር አቋራጭ አውቶቡሶች መስመራቸውን ይዘው ተሰልፈው የምእመናንን መምጣት ይጠባበቃሉ፡፡

የሐዊረ ሕይወት መርሐ ግብር በድምቀት ተካሔደ

ማኅበረ ቅዱሳን ለ5ኛ ጊዜ ያዘጋጀውን የሐዊረ ሕይወት መርሐ ግብር ደብረ ዘይት በሚገኘው ደብረ መድኃኒት ኢየሱስ ቤተ ክርስቲያን ታኅሳስ 6 ቀን 2006 ዓ.ም. ከ 5000 ምዕመናን በላይ በተገኙበት አካሔደ፡፡ ዝርዝሩን እንደደረሰን እናቀርባለን፡፡

“ግብረ ፊልጶስ” የተሠኘ ሲምፖዚየም እንደሚዘጋጅ ተገለጸ

ታኅሣሥ 05 ቀን 2006 ዓ.ም.

በእንዳለ ደምስስ

 

“ግብረ ፊልጶስ – ሐዋርያዊ ጉዞ በኢትዮጵያ በቀድሞው፤ በመካከለኛውና በአሁኑ ዘመን” በሚል መንፈሳዊ ጉባኤ በማኅበረ ቅዱሳን ትምህርትና ሐዋርያዊ አገልግሎት ዋና ክፍል የስብከተ ወንጌል ማስፋፊያ አማካይነት ሲምፖዚየም እንደሚዘጋጅ ተገለጸ፡፡ Baptism

 

ተኅሣሥ 12 እና 13 ቀን 2006 ዓ.ም. ከቀኑ 8፡00 ሰዓት ጀምሮ በቅድስት ሥላሴ መንፈሳዊ ኮሌጅ ስብከተ ወንጌል አዳራሽ በሚካሔደው ሲምፖዚየም ላይ ከዚህ በፊት በተልተሌ፤ ጂንካ፤ ከረዩ፤ መተከልና ግልገል በለስ አካባቢዎች ተጠምቀው የእግዚአብሔር ልጅነትን ያገኙ ምእመናን በአካል በመገኘት በጉባኤው ላይ አሁን ያሉበትን ሁኔታ ያቀርባሉ፡፡

የመስቀል በዓል አከባበር በዩኔስኮ ቅርስነት ተመዘገበ

 ኅዳር 26 ቀን 2006 ዓ.ም.

በእንዳለ ደምስስ

  • የመስቀል በዓል አከባበር ኢትዮጵያ በዩኔስኮ ካስመዘገበቻቸው 10 ቅርሶች መካከል የመጀመሪያው የማይዳሰስ ቅርስ በመባል መመዝገቡን አስመልክቶ የቅርስ ጥናትና ጥበቃ ባለሥልጣን ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጠ፡፡

 0202023 1
የኢትዮጵያ የቅርስ ጥናትና ጥበቃ ባለሥልጣን የኢትዮጵያ የመሰቀል በዓል አከባበር በተባበሩት መንግሥታት የትምህርት፤ የሳይንስና የባሕል ድርጅት (ዩኔስኮ) በማይዳሰሱ ቅርሶች (Intangible) በቅርስነት መመዝገቡን አስመልከቶ ኅዳር 26 ቀን 2006 ዓ.ም. በባለሥልጣኑ አዳራሽ ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጠ፡፡