የማቴዎስ ወንጌል
ሰኔ 16 ቀን 2006 ዓ.ም.
ምዕራፍ ሁለት
በዚህ ምዕራፍ ውስጥ የምንረዳውና የምንገነዘበው ጌታ በይሁዳ ቤተልሔም በንጉሥ ሄሮድስ ዘመን እንደተወለደ እንረዳለን፡፡ ቤተልሔም ማለት ቤተ ኅብስት ማለት ነው፡፡ ስምዋም የተሰየመው ካሌብ ኤፍራታ የተባለች ሚስት አግብቶ ወንድ ልጅ ከኳ በወለደ ጊዜ እንጀራ እገባ እገባ ብሎት ስለነበር የልጁን ስም ልሔም /ኅብስት/ አለው፡፡ በልሔም ቤተልሔም ተብላለች፡፡

የደብረ ሊባኖስ አቡነ ተክለ ሃይማኖት አንድነት ገዳም ያጋጠሙትን በርካታ ችግሮች ለመታደግ ዘላቂ መፍትሔ መሻት እንደሚገባ ሰኔ 8 ቀን 2006 ዓ.ም. በጠቅላይ ቤተ ክህነት ስብከተ ወንጌል አዳራሽ በተካሔደ የገቢ ማሰባሰቢያ መርሐ ግብር ጥሪ ቀረበ፡፡
በደብረ ሊባኖስ አቡነ ተክለ ሃይማኖት አንድነት ገዳም በ2004 ዓ.ም. በገዳሙና በማኅበረ ቅዱሳን ባለሙያዎች ተጠንቶ የቀረበው የገዳሙ ሁለንተናዊ የልማት ፕሮጀክት ተግባራዊ በመሆን ላይ እንደሚገኝ የገዳሙ የልማት ኮሚቴ ገለጸ፡፡
የምሥራቅ ሐረርጌ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ የነበሩት ብፁዕ አቡነ አብርሃም በግንቦት ወር 2006 ዓ.ም. የቅዱስ ሲኖዶስ ምልአተ ጉባኤ ባስተላለፈው ውሳኔ መሠረት የምዕራብ ጎጃም ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ሆነው በመዛወራቸው አዲሱን መንበረ ጵጵስና ተረክበዋል፡፡
ከግንቦት 30 ቀን 2006 ዓ.ም. ጀምሮ ለሁለት ቀናት በመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ስብከተ ወንጌል አዳራሽ ሲካሔድ የቆየው በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የሰንበት ትምህርት ቤቶች ማደራጃ መምሪያ ሀገር አቀፍ የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት 3ኛ ጠቅላላ ጉባኤ ሰኔ 1 ቀን 2006 ዓ.ም. የአቋም መግለጫ በማውጣት ተጠናቋል፡፡