የመምህር አካለ ወልድ የሐዲስ ኪዳን የመጻሕፍት ትርጓሜ ት/ቤት የበግ ማድለብ ፕሮጀክት ተግባራዊ ሊደረግ ነው
መጋቢት 9 ቀን 2007 ዓ.ም
ከደሴ ማእከል
የደቡብ ወሎ ሀገረ ስብከት ከ20 በላይ የወረዳ ቤተ ክህነት ሲኖሩት፤ እነዚህም ብዛት ያላቸው ጥንታውያን ገዳማትና አድባራትን እንዲሁም የአብነት ት/ቤቶችን አቅፎ የያዘ ነው፡፡ ሀገረ ስብከቱ ካሉት ጥንታውያን የአብነት ት/ቤቶች የቦሩ ሥላሴ የመምህር አካለ ወልድ የሐዲስ ኪዳን የመጻሕፍት ትርጓሜ ት/ቤት አንዱ ነው፡፡