አምልኮተ ሰይጣን – ፍጻሜ “ተሐድሶ”?
ባለፉት ተከታታይ ዕትሞች ስለ ተሐድሶ መናፍቃን እንቅስቃሴ አጠቃላይ ሁኔታ እና የትኩረት አቅጣጫዎች እንዳ ቀረብንላችሁ ይታወቃል፡፡ በዚህ ዕትም ደግሞ የተሐድሶ መናፍቃን ግብ ምን እንደሆነ እናስነብባችኋለን፤ መልካም ንባብ ይሁንላችሁ፡፡
እሱባለው በለጠ የተባሉ ጸሐፊ “የገሃነም ደጆች ፕሮቴስታንታዊ ጅሃድ በኢትዮጵያዊነት – ተዋሕዶነት ላይ ሲፋ ፋም” በሚለው መጽሐፋቸው አውሮፓ ውያን፣ የካቶሊክና የፕሮቴስታንት እንዲሁም የተሐድሶ መናፍቃን የኢት ዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስ ቲያንን ለማጥቃት የፈለጉበትን ምክን ያት ሲገልጡ “ፈረንጆች ሃይማኖታ ችንን ከገደሉ፣ ቅድስት ኢትዮጵያን በባርነት ለመያዝ ቀላል መሆኑን ስለ ሚያውቁ ነው ቤተ ክርስቲያንን የጥ ቃት ዒላማቸው ያደረጓት” (ገጽ ፳፯) ብለዋል፡፡ በተጨማሪም “ሁሉም ወራሪ ዎች ከግራ ይምጡ ከቀኝ፣ በነጮችም ይፈጸሙ በዐረብ/ቱርክ፣ ወረራው በጦር ይሁን ወይም በሐሳብ፣ ሁሉም ወራሪዎች የጥቃታቸው ዋና ዒላማ የሚያደርጓት የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያንን ነው፡፡ ግን ሁሉም ወራሪዎች ድል የተደረጉት የአንድነትና የነጻነት ምንጭ በሆነችው በዚች መከረኛ ቤተ ክርስቲያን ነው” (ገጽ ፳፫-፳፬) በማለት ጽፈዋል፡፡