Author Archive for: mkit
About Mahibere Kidusan
This author has not written his bio yet.
But we are proud to say that Mahibere Kidusan contributed 1445 entries already.
Entries by Mahibere Kidusan
በአልባሳት ማሰባሰቢያ መርሃግብሩ የመጀመሪያ ቀን ከ175ዐ በላይ አልባሳት ተሰበሰበ
ለመነኮሳትና አብነት ተማሪዎች የአልባሳት ማሰባሰቢያ መርሐግብር ተዘጋጀ።
የጥምቀት በዓል ፋይዳና ተግዳሮቶቹ
በስምንት ዓመት የጎንደር ቆይታዬ በየዓመቱ በዓሉን የመካፈል ዕድል አግኝቻለሁ። እያንዳንዱ ዓመት የየራሱ የሆነ ለየት ያሉ ትዕይንቶች ነበሩት። በአጠቃላይ ግን የታዳሚው ቁጥር ለማመን በሚያስቸግር መልኩ ከዓመት ወደ ዓመት እየጨመረ መጥቷል። በሌላ መልኩ ደግሞ ወጣቱ በበዓሉ ላይ ያለው ተሳትፎ ለውጥም ከቤተ ክርስቲያን ሥርዓት አንፃር በጣም የሚበረታታ ነው። የመርካቶ ሌላኛዉ መልክ
መርካቶ የሚለውን ቃል እዚህ ጋር ስናነብ መቼም በየሕሊናችን የሚመጡ ብዙ የመርካቶ ሥዕሎች ይኖራሉ ፡፡ በተለይ ግርግሩ፣ ማጭበርበሩ፣ ሌብነቱ፣ በቀላሉ የማይገታዉ አመጹ፣ ምንም ነገር ፈልጎ የማይታጣበት መሆኑ፣ ቆሻሻው….በነዚህ ሁሉ ነገሮች እንደ መርካቶ ቅድሚያዉን የሚይዝ አካባቢ የሚኖር አይመስለኝም፡፡
የጌታችን የመድኀኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ በዓለ ጥምቀት በጃንሜዳ።
የ2003 ዓ.ም የጌታችን የመድኀኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ በዓለ ጥምቀት ዋዜማ የከተራ በዓል በታላቅ ድምቀት ተከብሯል። በዋናው በዓል ዋዜማ፥ ከሥርዓተ ቅዳሴው ፍጻሜ በኋላ ታቦታተ ሕጉ ከመንበረ ክብራቸው ተነስተው በየምዕራፉ በሊቃውንት አባቶች ስብሐተ እግዚአብሔር እየተደረሰ በሰንበት ት/ቤት አባላትና ምዕመናን መዝሙር እየተዘመረ ወደ ባሕረ ጥምቀቱ አምርተዋል። «እስመ ከመዝ ተድላ ለነ ወይደልወነ ከመ ንፈጽም ኲሎ ጽድቀ»
የጎንደር መንበረ መንግሥት መድኅኔዓለም ደብር አስተዳዳሪና የአራቱ ጉባኤያት /የብሉይ፣ የሐዲስ፣ የሊቃውንትና የመጻሕፍተ መነኮሳት/ የጉባኤ መምህር ከሆኑት ከሊቀ ሊቃውንት ዕዝራ ሐዲስ ጋር የጥምቀትን በዓል አስመልክተን በ09/05/03 ዓ.ም አጭር ቃለ ምልልስ በስልክ አድርገናል፡፡ ለሊቀ ሊቃውንት ዕዝራ ሐዲስ ከፍተኛ ምስጋናችንን እያቀረብን ለአንባቢዎቻችን የታላቁን ሊቅ ቃለ ምልልስ በማቅረብ እንኳን አደረሳችሁ እንላለን፡፡ መልካም ንባብ፡፡ ተረት…………ተረት (ለህጻናት)
ልጆች ዛሬ አንድ ተረት ይዤላችሁ ቀርቤአለሁ፡፡ አንድ ጊዜ ምን ሆነ መሰላችሁ ፀሐይና ነፋስ ረጅም መንገድ አብረው ጉዞ ጀመሩ፡፡ እነዚህ ጓደኛሞች አብረው እየሔዱ ጨዋታ አንስተው ሲያወሩ ነፋስ ፀሐይን አንድ ጥያቄ ጠየቃት «ሰዎች የምትፈልጊውን ነገር እንዲያደርጉልሽ የምታደርጊያቸው በምንድን ነው?» ሲል ነፋስ ጠየቃት ፀሐይም የነፋስን ጥያቄ ሰማችና «እኔማ ከሰዎች የምፈልገውን መጠየቅ ብፈልግ በጣም ቢቆጡ፣ ቢሳደቡ እንኳን ቀስ አድርጌ በትህትና በፍቅር ረጋ ብዬ እጠብቃቸውና የምፈልገውን እንዲሰጡኝ /እንዲያደርጉልኝ/ አደርጋለሁ» አለችው፡፡ ነፋስ ወዲያውኑ ቀበል አደረገና «በጣም ተሳሳትሽ የምን መለማመጥ? የምትፈልጊውን ለማግኘት በጉልበት መጠቀም ነው እንጂ» አለ፡፡ «ፀሐይ እንደሱማ አይቻልም» አለች፡፡
