Entries by Mahibere Kidusan

የደቡብ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ከምእመናን ጋር ተወያዩ።

በተ/ሥላሴ ጸጋ ኪሮስ

በሐዋሳ ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን የተነሳው አለመግባባት አሁንም ቀጥሎ ማክሰኞ በ08/06/03 ዓ.ም በቤተ ክርስቲያን ውስጥ በተፈጠረው ግጭት ወጣቶችና ምእመናን ጉዳት ደርሶባቸዋል። እርሱን ተከትሎ ያለመግባባቱን ተዋናዮች ሰብስበው ያናገሩት የደቡብ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ክቡር አቶ ሽፈራው ሽጉጤ ተቃውሞን ሰላማዊ በሆነ መልኩ ብቻ መግለጥ እንደሚቻል አሳስበዋል።

በአንድ እጅ ማጨብጨብ እንዳይሆን

ከመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ጽ/ቤት እና ከየአህጉረ ስብከቱ ሊቃነ ጳጳሳት የስብከተ ወንጌል ፍቃድ ሳይኖራቸው በየቤተ ክርስቲያኑ ዐውደ ምሕረት በሕዝበ ክርስቲያኑ መካከል እየተገኙ እንሰብካለን እናስተምራለን በማለት የቅድስት ቤተ ክርስቲያንን ሥርዓትና መመሪያ በሚጥሱ  ሕገወጥ ሰባክያን፤ ከቤተ ክርስቲያን ዕውቅናና ፈቃድ ውጪ በጉባኤ ሊቃውንት ያልታዩና ያልተመረመሩ የተለያዩ የኅትመት ውጤቶች፤ መጻሕፍት፣ የስብከት የመዝሙር የምስል ወድምፅ /ኦዲዮ ቪዲዮ/ ካሴቶች እየተሠራጩ፤ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያንን መሠረተ እምነት፣ ሥርዓትና ትውፊት የሚጥሱ ተግባራት ሲፈጸሙ ይታያል፡፡

“የእኛ ግዴታ ሲኖዶስ ያወጣውን ሕግ ማስከበር ነው” ሊቀ ኅሩያን ዓለም እሸት ገ/ጻድቅ

በተ/ሥላሴ ጸጋ ኪሮስ   

hawassakidusgebrieltiks.jpgባለፈው ጊዜ በሐዋሳ ከተማ በተለይም ደብረ ምሕረት ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን የተፈጠሩትን ጉዳዮች አስመልክቶ ከሀገረ ስብከቱ ሥራ አስኪያጅ ሊቀ ኅሩያን ዓለም እሸት ገ/ጻድቅ ጋር ያደረግነውን ውይይት የመጀመሪያ ክፍል የሐዋሳ ጉዳይ 1 በሚል ርዕስ አቅርበንላችሁ ነበር። የውይይታችን ቀጣይ ክፍል ደግሞ እነሆ፤ መልካም ንባብ። (ፎቶ፦ ሐዋሳ ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ግቢ ውስጥ ከሚገኙት ጥቅሶች መካከል)

የነነዌ ህዝቦች (ለህጻናት)

        በአንድ ወቅት ስሙ ዮናስ የተባለ ሰው ነበር፡፡ ከእለታት አንድ ቀን እግዚአብሔር አምላክ ለዮናስ እንዲህ አለው፡፡ «ወደ ነነዌ ከተማ ሂድ ለሕዝቡም በምትሰሩት የኃጢዓት ሥራ በጣም አዘኜባችኋለሁ፡፡ ይኼንን የምትሠሩትን ሥራ ካላቆማችሁ ከተማዋን አጠፋታለሁ» ብለህ ንገራቸው አለው፡፡ ነገር ግን ዮናስ እግዚአብሔር ያዘዘውን ማድረግ አልፈለገም፤ እየሮጠ ማምለጥ እና ከእግዚአብሔር መደበቅ ፈለገ ስለዚህም ዮናስ ከነነዌ ከተማ በተቃራኒው ወደ ምትገኘው አገር በመርከብ መሔድ ጀመረ፡፡

የሐዋሳ ጉዳይ 1

hawassakidusgebriel.jpgባለፉት ጥቂት ወራት በሐዋሳ ከተማ፥ በተለይም ደብረ ምሕረት ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን በርካታ ችግሮች ሲከሰቱ ቆይተዋል። ያለውን ሁኔታ በተመለከተ ወደ ሐዋሳ የተጓዘው ሪፖርተራችን ተሥፋሥላሴ የሀገረ ስብከቱን ሥራ አስኪያጅ፥ የዋሳ ደብረ ምሕረት ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን አስተዳዳሪንና ምእመናንን አናግሮ ዘገባ አጠናቅሯል።
በመጀመሪያ ከሀገረ ስብከቱ ሥራ አስኪያጅ ከሊቀ ኅሩያን ዓለም እሸት ገ/ጻድቅ ጋር የተደረገውን ቃለ መጠይቅ በሁለት ክፍል እናቀርባለን። በቀጣይነት በቦታው ያለውን ዝርዝር ሁኔታ የሚመለከት ሐተታዊ ጽሑፍ እንደ እግዚአብሔር ፈቃድ ለማስነበብ እንሞክራለን።

ትንሣኤ ግዕዝ

 

/ርት ፀደቀ ወርቅ አስራት

የጥንቱ ውበቱ

ጭራሽ ተዘንግቶ፣

ለብዙ ዘመናት

የሚያስታውስ አጥቶ፣

ተዳክሞ ቢያገኙት

ግዕዝ አንቀላፍቶ፣ 

ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ እና የ«ተሐድሶዎች» ቅሰጣ

                                    በእደማርያም ንርአዩ

ምድራችን እስከ ዕለተ ምጽአት ከመልካም ስንዴው ጋር እንክርዳዱን ማብቀሏ፤ ከየዋሁ በግ ጋር ተኩላውን ማሰለፏ፤ ከንጹሐን ሐዋርያት መካከል ይሁዳን ማስገኘቷ አይቀርም፡፡ እንክርዳዱ እንዳይነቀል ከስንዴው ጋር አብሮ በቅሎ፣ ተኩላው እንዳይጋለጥ በግ ይመስል ዘንድ ለምድ ለብሶ ከስንዴው ጋር ልዘናፈል፣ ከበጉም ጋር ልመሳሰል ብለው ያልሆኑትን ለመሆን እየታገሉ ለዓላማቸው መስለው የሚሠሩ ተቆርቋሪም ሆነው የሚቀርቡ በማባበል ቃል የሚጎዱ ከፍጥረት ጅማሬ እስከ ዘመን ፍጻሜ፤ ከመላእክት ከተማ እስከ ደብረ ዘይት ተራራ ጌታችን እስከሚገለጥበት ቦታ ከገነት እስከ ዛሬዋ መቅደስ ስተው እያሳቱ ክደው እያስካዱ ከዚህ ዘመን ደርሰዋል፡፡

ከ7500 በላይ አልባሳት ተሰበሰበ

በፈትለወርቅ ደስታ
«ሁለት ልብሶች ያሉት…..» በሚል መሪ ቃል የተጀመረው የአልባሳት ማሰባሰቢያ መርሐ ግብር የቀጠለ ሲሆን የመጀመሪያውን ቀን ጨምሮ እስከ እሁድ ጥር 29 ቀን 2003 ዓ.ም ድረስ ባሉት ቀናት ከ7500 በላይ አልባሳት፣ ከ10 በላይ ጣቃ የተለያዩ ብትን ጨርቆችና ለመነኮሳት የሚሆኑ አልባሳት እንደተሰበሰበ ታውቋል፡፡

በዚህ መርሐ ግብር አልባሳቱ ከአዲስ አበባ፣ ከአዲስ ዓለምና ከኳታር እንደተሰበሰቡ ለማወቅ ተችሏል፡፡ በአልባሳት መደገፍ ያልቻሉ በርካታ ምዕመናንም መርሐ ግብሩን በገንዘብ በመደገፍ ተሳትፎ እያደረጉ ነው፡፡

‹‹በሰውም ምሳሌ ሆኖ ራሱን ዝቅ አደረገ፡፡›› ፊልጵስዩስ 2፡6

                                                   በማሞ አየነው
 
እነሆ የጨለማው ዘመን አለፈ፡፡ በጨለማ ይኖሩ የነበሩ ሕዝቦችም ብርሃን አዩ፡፡ መላእክትና ኖሎት /እረኞች/ በአንድነት እግዚአብሔርን አመሰገኑ፡፡ እርቅ በሰውና በእግዚአብሔር መካከል ተደረገ፡፡ የሰው ምኞትም ተፈፀመ፡፡ ሰላም፣ ፍቅር፣ ተስፋ በምድር ሰፈነ፡፡ እነዚህ ሁሉ በክርስቶስ የልደት ገፀ በረከት የተገኙ ናቸው፡፡ ከሰው ልጅ ውድቀት በኋላ በምድር የሚኖሩ ሰዎች በቀቢጸ ተስፋ፣ ሰላም በማጣት ከእግዚአብሔር ፈቃድ ውጭ ሆነው ለብዙ ሺህ ዓመታት ኖረዋል፡፡ የነቢያት ጾም ጸሎት፣ የካህናት መሥዋዕት ምድርን ከኃጢአት ሊያነጻ አልቻለም፡፡ ምድርን ከኃጢአት የሚያነጻት ወልደ እግዚአብሔር ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ብቻ በመሆኑ እነሆ አምላክ ሰው ሆነ፡፡ መጥምቀ መለኮት ቅዱስ ዮሐንስ ‹‹እነሆ የዓለምን ኃጢአት የሚያስወግድ የእግዚአብሔር በግ›› ዮሐ 1፡29  በማለት ምስክርነቱን ሰጥቷል፡፡ ስለዚህም ነው ጌታችንና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በአጭር ቁመት በጠባብ ደረት ተወስኖ በፍፁም ትህትና የሰውን ልጅ ሥጋ ለብሶ ሰው መሆንን የመረጠው፡፡

ከታሪክ አንድ ገጽ

እንደዚህ ሆነ፡፡
በአንዲት መንደር ውስጥ አንድ ሰው ነበረ፡፡ አንደበቱ ከጸሎት እጁ ከምጽዋት ልቡ ከጠዋሐት ተለይቶ የማያውቅ፤ ሰው ተጣላ ማን ያስታርቅ፣ ልጅ አገባ ማን ይመርቅ ቢባል በመጀመሪያ የሚጠራው እርሱ ነው፡፡