Entries by Mahibere Kidusan

በማኅበረ ቅዱሳን የኅትመት ውጤቶች ላይ ተጥሎ የነበረው የአባ ሠረቀ ሕገ ወጥ ደብዳቤ ተሻረ

ተ/ሥላሴ ጸጋ ኪሮስ
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የሰንበት ት/ቤቶች ማደራጃ መምሪያ ሓላፊ ቆሞስ አባ ሠረቀ ብርሃን ወልደ ሣሙኤል ማኅበረ ቅዱሳን የሚያሳትማቸው መጽሔትና ጋዜጣ ለኅትመት እንዳይውሉ የጻፉት ሕገ ወጥ የእግድ ደብዳቤ እንዲነሣ መደረጉን የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ጽ/ቤት አስታወቀ፡፡

Capital “C”

በድንቅነሽ ጸጋዬ

ሰኔ 1/2003 ዓ.ም.     

capital C

 
ዛሬ ደግሞ እንደ ሙአለ ሕፃናት ተማሪዎች Capital “C”ን እዚህ ምን አመጣት ትሉኝ ይሆናል፡፡ እኔም የትኩረት አቅጣጫዬ ስለ Capital “C” እንዳልሆነ እርግጠኛ ነኝ፡፡ ስለ ትምህርት ሲነሣ ወላጆቻችን ሀ ብለው የጀመሩት በተለምዶ ቄስ ትምህርት ቤት ብለን በምንጠራቸው ሲሆን፥ ትምህርቱም ይሰጥ የነበረው የሁሉም አፍ መፈቻ ቋንቋ ባይሆንም አብዛኛው ሰው ይግባበት በነበረው የአማርኛ ቋንቋ ፊደል ሀሁ፣ አቡጊዳ፣ መልዕክተ ዮሐንስ ዳዊት…ወዘተ፥ ዘመናዊውን የአስኳላ ትምህርት ከመቀጠላቸው በፊት፥ እንደተማሩ እናውቃለን፡፡ ለዚህም ቅድስት ቤተ ክርስቲያናችን ዋነኛ የትምህርት ማዕከል ሆና አገልግላለች፡፡

እናትና አባትህን አክብር (ለህጻናት)

ግንቦት 30/2003 ዓ.ም.

                                  በአዜብ ገብሩ
“እግዚአብሔር አምላክህ በሚሰጥህ ምድር ላይ ዕድሜህ እንዲረዝም፣ መልካምም እንዲሆንልህ እናትና አባትህን አክብር፡፡” ዘዳግም 5÷16
እንደምን ሰነበታችሁ ልጆች ደህና ናችሁ የዛሬው ጽሑፋችን እናትና አባትን ስለማክበር ነው በደንብ ተከታተሉን፡፡

“አብዝቶ የመመገብ ጣጣው”

  (በቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ)
ግንቦት 30/2003 ዓ.ም.

ዲ/ን ሽመልስ መርጊያ

መግቢያ

ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ የዮሐንስን ወንጌል በተረጎመበት በ21ኛው ድርሳኑ “ ጌታችን በእናታችን በቅድስት ድንግል ማርያም ጥያቄ በቃና ሰርግ ላይ ስለምን ውሃውን ወደ ወይን ጠጅነት እንደቀየረው  ከአብራራ በኋላ ከዛሬ 1500 ዓመት በፊት በአሁኑ ጊዜ እንደ አዲስ ግኝት ተደርገው የሚታዩትን አብዝቶ በመመገብ የሚመጡትን የጤና ጉድለቶች ጽፎልን እናገኛለን ፡፡ ጽሑፉ ተተርጉሞ እንዲህ ቀርቦአል።

ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ውሃውን ወደ ወይን ጠጅነት ያኔ እንደቀየረ ዛሬም እኛን ድካማችንንና እንደ ወራጅ ውሃ በአንድ ቦታ ጸንቶ መቆየት የተሣነውን የሥጋ ፈቃዳችንን ከመቀየር አልተቆጠበም ፡፡ ዛሬም አዎን ዛሬም ልክ እንደ ወራጅ ውሃ ቀዝቃዛ ፣የፈጠነና ፣ ያልተረጋጋ ጠባይ ያላቸው ሰዎች አሉ ፡፡ እነዚህን ፈቃዶቻችንን ወደ ጌታችን እናምጣቸው ፤ እርሱ ወደ ወይንነት ይቀይራቸዋል፡፡ ከዚያም በኋላ ውኃ ሆነው ከእንግዲህ አይቀጥሉም ፡፡ ነገር ግን ለራሳቸውና ለሌሎች ደስታን የሚሰጡ አካላት ይሆናሉ ፡፡

በማ/ቅዱሳን የአሜሪካ ማዕከል ዓመታዊ ጠቅላላ ጉባኤ ውሳኔዎችን በማሳለፍ ተጠናቀቀ።

 
(የአሜሪካ ማዕከል፤ አትላንታ፤ ጆርጂያ)፦ “የቤተ ክርስቲያናችንን ህልውና መጠበቅ የሁላችንም ኃላፊነት ነው” በሚል መሪ ቃል ግንቦት 20, 21 እና 23/ 2003 ዓ.ም ሲካሔድ የቆየው በማ/ቅዱሳን የአሜሪካ ማዕከል ዓመታዊ ጠቅላላ ጉባኤ ውሳኔዎችን በማሳለፍ እና የ2004 ዓ.ምሕረትን ዕቅድ በማጽደቅ ተጠናቀቀ።

ቅዱስ ጳውሎስ(ለሕፃናት)

ግንቦት 23 2003 ዓ.

በእመቤት ፈለገ

እንደምን ሰነበታችሁ ልጆች? ደህና ናችሁ? ዛሬ ስለ አንድ ትልቅ የቤተ ክርስቲያን ሐዋርያ ታሪክ እንነግራችኋለን በደንብ ተከታተሉን፡፡
 
በድሮ ጊዜ በኢየሩሳሌም ከተማ የሚኖር ክርስቲያኖችን የሚጠላና በእነርሱ ላይ ክፉ ሥራ የሚሠራ ሳውል የሚባል ሰው ነበረ፡፡ ደማስቆ ወደምትባል ከተማም ክርስቲያኖችን ሊገድል ጉዞ ጀመረ፡፡

የምዕራብ ጎጃም ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ በርናባስ አጭር የሕይወት ታሪክ

ከባሕር ዳር ማዕከል

ግንቦት23፣ 2003ዓ.ም

ብፁዕ አቡነ በርናባስ ግንቦት 20 ከምሽቱ 3.00 ማረፋቸው ይታወሳል፡፡

ብፁዕ አቡነ በርናባስ፣ የካቲት 12 2003 ዓ.ምየብፁዕነታቸው የቀብር ሥነ ሥርዓት ግንቦት 22 ቀን 2003 ዓ.ም የተፈጸመ ሲሆን በሥርዓቱ ላይ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ጳውሎስ ፓትርያርክ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ብፁዕ አቡነ ገሪማ፣ ብፁዕ አቡነ ሕዝቅኤል፣  ብፁዕ አቡነ አረጋዊ፣ ብፁዕ አቡነ ኤልሣዕ  ብፁዕ አቡነ ሄኖክ፣ ብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ፣ ብፁዕ አቡነ ማርቆስ እንዲሁም የአማራ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ አያሌው ጎበዜና የክልሉ ባለ ሥልጣናት፣ ከአዲስ አበባ የመጡ የደብር አስተዳዳሪዎች፣ የቅድስት ሥላሴ ኮሌጅ የመጻሕፍት ትርጓሜ መምህር የሆኑት መምህር ደጉ ዓለም ካሣ፣  የማኅበረ ቅዱሳን ሥራ አመራር ጉባኤ ጸሐፊ አቶ ዘላለም አጥናፉ እንዲሁም ሌሎች በርካታ እንግዶችና ምዕመናን ተገኝተዋል፡፡

ለአባ የትናንቱ

ዲያቆን ሄኖክ ኃይሌ

ግንቦት 23፣2003ዓ.ም

ያለ ማወቅ ጽልመት ሀገሩን ሲወርሰው ቅዱስ ተክለ ሃይማኖት

ማን ነበር ትውልዱን በወንጌል ያረሰው?

አባ ተክለ ሃይማኖት አባ የትናንቱ

ትዝ አለኝ ተጋድሎው ውል አለኝ ሕይወቱ

በቆላ በደጋ የተንከራተትኸው

የሃይማኖትን ተክል ዞረህ የተከልኸው