እናትና አባትህን አክብር (ለህጻናት)

ግንቦት 30/2003 ዓ.ም.

                                  በአዜብ ገብሩ
“እግዚአብሔር አምላክህ በሚሰጥህ ምድር ላይ ዕድሜህ እንዲረዝም፣ መልካምም እንዲሆንልህ እናትና አባትህን አክብር፡፡” ዘዳግም 5÷16
እንደምን ሰነበታችሁ ልጆች ደህና ናችሁ የዛሬው ጽሑፋችን እናትና አባትን ስለማክበር ነው በደንብ ተከታተሉን፡፡
ልጆች ከአሥርቱ ትዕዛዛት መካከል አንዱ እናትና አባትህን አክብር የሚለው ነው፡፡ እግዚአብሔር እናትና አባታችንን ካከበርን ሽልማት እንደሚሰጠን ነግሮናል፡፡ ሽልማቱም በምድር ላይ ስንኖር ዕድሜያችን ረዥም እንደሚሆንና፤ በዚህ ዕድሜያችንም መልካም የሆነ ነገር እንደሚያደርግልን ነው፡፡ ለእናትና ለአባታችን ስንታዘዝ እግዚአብሔር ሽልማት እንደሚሸልመንና በእኛ እንደሚደሰት ሁሉ ካልታዘዝን ደግሞ ያዝንብናል፡፡ አዎ! እናትና አባቱን የማያከብር፣ ስድብ የሚሳደብ፣ በትዕቢት ዐይን እናትና አባቱን የሚመለከት ልጅ እግዚአብሔር ደስ አይሰኝበትም፡፡ስለዚህ ልጆች እናትና አባታችን ማክበር ይገባል ማለት ነው፡፡ እናትና አባታችን ማክበር እንዳለብን ካወቅን እንዴት ነው የምናከብራቸው?
 

1.    በመታዘዝ “ልጄ ሆይ የአባትህን ምክር ስማ የእናትህንም ትእዛዝ ቸል አትበል፡፡” ምሳ.1÷8
2.    ጥሩ ልጅ በመሆን
3.    አክብሮት የተሞላበት ንግግር በመናገር
4.    በመውደድ

እንግዲህ ልጆች እናትና አባትን ማክበር ከእግዚአብሔር ዘንድ ሽልማት የሚያሰጥ መልካም ሥራ ነውና እናትና አባታችንን ልናከብር ይገባል ማለት ነው፡፡ ጌታችን ራሱ እናቱ ድንግል ማርያምን  ያከብር ነበር፤ ይታዘዛትም ነበር፡፡ እኛም እርሱን ምሳሌ አድርገን ልናከብራቸውና ልንታዘዛቸው ይገባል፡፡ እርሱም እኛን ይወደናል፡፡
ወስብሐት ለእግዚአብሔር