Entries by Mahibere Kidusan

ምዕዳነ አበው

በዲ/ን ኅሩይ ባየ እና በደረጀ ትዕዛዙ
 ሰኔ 17 ቀን 2003 ዓ.ም
/ምንጭ፦ ስምዐ ጽድቅ ጋዜጣ ከግንቦት1-15፣ 2003 ዓ.ም/ 
 
የቅዱስ ሲኖዶስ የርክበ ካህናት ጉባኤ ከግንቦት 10-16 ቀን 2003 ዓ.ም ሲካሔድ ቆይቶ ውሳኔዎችን በማሳለፍ ተጠናቋል፡፡ ስለ ጉባኤው ሒደት አስተያየታቸውን እንዲሰጡን፤ ተሳታፊ ከነበሩት የቅዱስ ሲኖዶስ አባላት በተለያዩ ጉዳዮች ላይ ይመለከታቸዋል ብለን ያሰብናቸውን ብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳት አነጋግረን የዚህ ዕትም የአብርሃም ቤት እንግዳ አድርገናቸዋል፡፡

«ያሳለፍናቸው ውሳኔዎች በሥራ ላይ መዋል አለባቸው፡፡»

  የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊ ብፁዕ አቡነ ሕዝቅኤል

ስምዐ ጽድቅ፡- የግንቦቱ ቅዱስ ሲኖዶስ ጉባኤ የርክበ ካህናት ጉባኤ ስለተወያየባቸው አጀንዳዎች ቢገልጹልን? 

ብፁዕ አቡነ ሕዝቅኤል፡- ተወያይተን ውሳኔ ያሳለፍንባቸው አጀንዳዎች ወደ ዐሥራ ሦስት ይሆናሉ፡፡ የብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርኩ የጉባኤ መክፈቻ ንግግር፣ የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊ ዓመታዊ የሥራ ክንውን፣ በቅርቡ ለጠቅላይ ቤተ ክህነት ሠራተኞች ስለተደረገው የደመወዝ ጭማሪ፣ የኢትዮጵያ ታላቁ የሕዳሴ ግድብ ግንባታ፣ የሲዳማ ሀገረ ስብከት ችግር፣ መንፈሳዊ ተቋማትን በተመለከተ፣ የልማት እና ክርስቲያናዊ ተራድኦ ኮሚሽን ኤች አይ ቪ/ ኤድስ መከላከያና መቆጣጠሪያ መምሪያ ሥራ አፈጻጸም፣ ልማትን በተመለከተ፣ የስብከተ ወንጌል ጉዳይ፣ የሊቃነ ጳጳሳት ዝውውር፣ በሰንበት ት/ቤቶች ማደራጃ መምሪያ ሓላፊ እና በማኅበረ ቅዱሳን የተፈጠረውን አለመግባባት በተመለከተ፣ የቀጣዩ ቋሚ ሲኖዶስ አባላት ምርጫና ልዩ ልዩ የሚሉ ናቸው፡፡
 

አጭሩ ዘኪዮስ(ለሕፃናት)

ሰኔ11 ፣2003 ዓ.ም

አዜብ ገብሩ

ዘኪዮስ የሚባል አጭር ሀብታም ሰው ነበረ፡፡ ኢየሱሱ ክርስቶስን ለማየት በጣም ይፈልግ ነበር፡፡ ምክንያቱም ስለ እርሱ ብዙ ነገር ሲነገር ይሰማ ስለነበረ ነው፡፡ ጌታችን በዛሬው ዕለት ኢያሪኮ ወደምትባለው ከተማ ይገባል ብለው ሰዎች ሲያወሩ ዘኪዮስ ሰማ፡፡

የግቢ ጉባኤያትን ተማሪዎች መንፈሳዊ ሕይወት ለማሳደግ የሚያስችል የንሰሐ አባቶች ሴሚናር ተካሔደ

በእንዳለ ደጀኔ

ሰኔ 10 ቀን 2003 ዓ.ም 

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን በሰንበት ት/ቤቶች ማ/መምሪያ ማኅበረ ቅዱሳን የግቢ ጉባኤያት ተማሪዎችን መንፈሳዊ ህይወት ለማሳደግ የሚያስችል የግቢ ጉባኤያት ተማሪዎች የንስሐ አባቶች ሴሚናር ተካሔደ፡፡

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ውስጥ የተሐድሶ እንቅስቃሴ አለን? ዓላማውና ስልቱስ ምንድን ነው?

ሰኔ 11 ቀን 2003 ዓ.ም

/ምንጭ፦ ስምዐ ጽድቅ ልዩ እትም ግንቦት 2003 ዓ.ም/

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን “መታደስ አለባት” የሚሉ ድምፆችን የሚያሰሙ አካላት አሳባቸውን በተለያዩ መንገዶች ማሰማት ከጀመሩ ውለው አድረዋል፡፡ እነዚህ አካላት በመጽሔቶች፣ በጋዜጦች፣ በመጻሕፍት፣ በበራሪ ወረቀቶች፣ በዓውደ ምሕረት ስብከቶችና በሚያገኟቸው አጋጣሚዎች ሁሉ ይኸን ጩኸታቸውን ማስተጋባቱን ተያይዘውታል፡፡ እንዲህ እያሉ ያሉትም “ኦርቶዶክሳውያን ነን” እያሉ በቤተ ክርስቲያኒቱ ውስጥ በተለያየ ቦታና ሓላፊነት ላይ ካሉና እንጀራዋን ከሚበሉ፣ ጥቂቶች እንዲሁም ደግሞ በኅቡእና በግልጽ በተለያየ መልክና ቅርጽ ራሳቸውን አደራጅተው ቤተ ክርስቲያኗ ሳትወክላቸው እርሷን ወክለው፣ “እኛም ኦርቶዶክስ ነን” በሚል ካባ ራሳቸውን ደብቀው እምነቷንና ሥርዓቷን “ይህ ሳይሆን ሌላ ነበር” እያሉ ፕሮቴስታንታዊ ትምህርትና መንፈስ የተዋረሳቸው ሰዎች ናቸው፡፡

መልአከ ገነት ኃይለ ማርያም ፋንታሁን አረፉ።

ከባህር ዳር ማእከል

ሰኔ 9 ቀን 2003 ዓ.ም

መልአከ ገነት ኃይለ ማርያም ፋንታሁንበባህር ዳር ከተማ በሚገኘው ፈለገ ገነት ቅዱስ ጊዮርጊስ ገዳምን ከ40 ዓመት በላይ በአስተዳዳሪነት ያገለገሉት መልአከ ገነት ኃይለ ማርያም ፋንታሁን በጠና ከታመሙ በኋላ በተወለዱ በ80 ዓመታቸው ግንቦት 30 ቀን 2003 ዓ.ም ከምሽቱ 2፡00 ሰዓት አርፈዋል። 

ሥርዓተ ቀብራቸው ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት ብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ፣ ብፁዕ አቡነ ኤልያስና ብፁዕ አቡነ ቶማስ፣ ብፁዕ አቡነ ማርቆስ እንዲሁም ወዳጅ ዘመድና ቤተሰቦቻቸው በተገኙበት በፈለገ ገነት ቅዱስ ጊዮርጊስ ገዳም በዕለተ ሐሙስ ሰኔ 2 ቀን 2003 ዓ.ም ከቀኑ 5፡30 ተፈጽሟል፡፡

ጰራቅሊጦስ(ለሕፃናት)

ሰኔ 07 2003 ዓ.

አዜብ ገብሩ

እንደምን ሰነበታችሁ ልጆች? ደህና ናችሁ? እንኳን ለበዓለ ጰራቅሊጦስ በሰላም  አደረሳችሁ፡፡

ከትንሣኤ በኋላ ያለው ሃምሳኛው ቀን ጰራቅሊጦስ ይባላል፡፡ ይህ ዕለት ጌታ ለሐዋርያት መንፈስ ቅዱስን ያወረደበት ዕለት ነው፡፡ ልጆች ጌታ ከሞት ከተነሣ በኋላ አስራ ሁለቱ ሐዋርያት በቅዱስ ማርቆስ እናት ቤት ከሰባሁለቱ አርድዕት አና ከሰላሳ ስድስቱ ቅዱሳን አንስት ጋር በመሆን ይጸልዩ ነበር፡፡ ጌታም በተለያየ ጊዜ እየተገለጸ ያስተምራቸው ነበር፡፡ አጽናኝ የሆነውን ቅዱስ መንፈስም እንደሚልክላቸው ይነግራቸው ነበር፡፡

አዲስ መንፈሳዊ ተውኔት ይመረቃል

በይበልጣል ሙላት

ሰኔ 6፣2003ዓ.ም

በማኅበረ ቅዱሳን የአዲስ አበባ ማዕከል የትምህርትና ኪነጥበባት ክፍል የተዘጋጀውና “አሻራ” የሚል ስያሜ የያዘው ተውኔት ይመረቃል፡፡

ተውኔቱ እሑድ ሰኔ 12 ቀን 2003 ዓ.ም ከቀኑ 8፡00 በማኅበረ ቅዱሳን ህንፃ እንደሚመረቅ የተገለጸ ሲሆን ከዚያ በኋላ ለምዕመናን ክፍት ይሆናል ተብሏል፡፡

በኦሞ ወንዞች ዙሪያ ተስፋ የሚያደርጉ ዓይኖች!

በማኅደረ ታሪኩና ተ/ሥላሴ ጸጋ ኪሮስ
ሰኔ 03፣ 2003 ዓ.ም 
 

Debub_Omo1.jpg

 
ከሐመር ብሔረሰብ አባላት ለአንዱ፣ የፈጠራችሁ ማን ነው? ብላችሁ ጥያቄ ብታቀርቡ በእምነት በጠጠረ፣ ጥያቄያዊ በሆነ ፊትና የዋሕ ልቡና “ቦርጆ ነዋ! ቦርጆ፣ ከእርሱ በረከት ያልተቋደሰ፣ በእርሱ እቅፍ ውስጥ የሌለ፣ እርሱ ያላበላው፣ እርሱ ያላጠጣው ማን አለ? እርሱ ሁሉን በፍቅር የሚንከባከብ፣ ሕፃናትን የሚያሳድግ የፍቅር አምላክ ነው” ይሏችኋል፡፡

በዚህም አያቆሙም “ቦርጆ በእኛ መካከል ሲኖር ነበር፣ በቆይታ አንዳንዶችDebub_Omo22.jpg በልባቸው ክፉ አስበው አስቀየሙት፣ ቦርጆን ገረፉት፣ መቱት፣ አቆሰሉት፡፡ እርሱም ከእንግዲህ ‘ከእናንተ ጋር ሆኜ /እየኖርኩ/ የማበላችሁ የማጠጣችሁ አይምሰላችሁ፡፡ ወደ ሰማይ እሄዳለሁ በልባችሁ ግን ለምኑኝ አበላችኋለሁ፣ አጠጣችኋለሁ’ ብሎን ሄዷል፡፡” በማለት ስለ አምላካቸው ያብራራሉ፡፡