Entries by Mahibere Kidusan

እንግዳ ተቀባዩ አባ ቢሾይ(ለሕፃናት)

ሐምሌ23፣2003 ዓ.ም
                                                                               አዜብ ገብሩ

እግዚአብሔርን ከሚፈሩ ጻድቅ ከሆኑ ሰዎች የተወለደ አባ ቢሾይ የሚባል አባት ነበረ፡፡ ይህ አባት ለቤተሰቦቹ ሰባተኛ እና የመጨረሻ ልጅ ነው፡፡ አንድ ሌሊት ምን ሆነ መሰላችሁ ልጆች የአባ ቢሾይ እናት ሕልም አየች የእግዚአብሔር መልአክ ተገለጸ፡፡ ጌታ እንዲህ ብሏል፤ “ያገለግለኝ ዘንድ ከልጆችሽ አንዱን ስጭኝ” እናቱም እንዲህ አለች “ሰባቱም ልጆቼ አሉ፤ የፈለግኸውን መርጠህ እንዲያገለግልህ ውሰድ”

መሠልጠን ማለት ግን ምን ማለት ነው?!

በዲ/ን ቴዎድሮስ በየነ

ሥልጣኔ ሲተነተን አንድ ገጽታ፣ አንድ መልክ፣ አንድ ወጥ ሳይሆን ብዙ መልኮች፣ ብዙ ገጽታዎች እንዳሉት ማጤን ይገባል፡፡

ሥልጣኔ የሰው ልጅ አካባቢውን ለኑሮ እንዲስማማው፣ እንዲመቸው ለማድረግና ለሕይወቱ የተመቻቸ ሥፍራ ለማድረግ የዕለት ተዕለት ተግባር ውስጥ ቀስ በቀስ የተከሰተ ነው፡፡ በዚህ ረገድ ሥልጣኔ ጥንትም የነበረ፣ ዛሬም ያለ፣ ለወደፊትም የሚኖር የሰው ልጅ የተፈጥሮ እንቅስቃሴ ነው፡፡ ሆኖም ግን ስለ ሥልጣኔ ብይን ሲሰጥ፣ ስለ መግለጫው ሲነገር፣ ስለ ጥቅሙ ሲዘመር፣ ስለ ግቡ /መዳረሻው/ ሲታተት፤ ሥልጣኔ ከቁሳዊ ነገር መሟላትና ከሥጋዊ ድሎትና ምቾት ጋር ብቻ ሲያያዝ ይስተዋላል፡፡ ለዚህም ይመስላል የሥልጣኔን ክስተት በዓይን በሚታዩ፣ አብረቅራቂና ሜካኒካዊ በሆኑ ነገሮች ብቻ እንድናይ ከታች ጀምሮ በትምህርት ቤት እንድንማረው የሆነው፡፡ በሚዲያ ዘወትር እንድንሰማው የተደረገው፡፡ከበደ ሚካኤል ስለ ሥልጣኔ ምንነት ሲናገሩ እንዲህ ይላሉ፡፡

«ጠቅላላ ጉባኤው አንድነታችንን ፍቅራችንን የምናጸናበት ነው፡፡» ዲ/ን ሙሉዓለም ካሣ

የአዲስ አበባ ማዕከል 17ኛ ጠቅላላ ጉባኤውን ሐምሌ 23 እና 24/ 2003 ዓ.ም ያደርጋል። ጉባኤውን በተመለከተ በማዕከሉ የአባላትና አገልግሎት ማስተባበሪያ ክፍል ኃላፊ ከሆኑት ዲ/ን ሙሉዓለም ካሣ ጋር ያደረግነውን ቆይታ ይዘን ቀርበናልና መልካም ንባብ።

ቅድስት ቤተ ክርስቲያን ከ15,000 በላይ የከፍተኛ ተቋማት ተማሪዎችን አስመረቀች።

ተ/ሥላሴ ጸጋ ኪሮስ
Temerakiwoch.JPG

ማኅበረ ቅዱሳን በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ትምህርታቸውን ሲከታተሉ የነበሩና በግቢ ጉባኤያት ትምህርተ ሃይማኖት ያስተማራቸውን ከ15,000 በላይ ተማሪዎች በአባቶች ቡራኬ አስመረቀ። ተመራቂዎች የአደራ ቃልም ተሰጥቷቸዋል።

በአዲስ አበባና አካባቢዋ በሚገኙ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ሲማሩ የነበሩ ተማሪዎች ዛሬ እሑድ ሐምሌ 17 ቀን 2003 ዓ.ም በጠቅላይ ቤተ ክህነት አዳራሽና በማኅደረ ስብሐት ልደታ ለማርያም ቤተ ክርስቲያን ተክለ ሳዊሮስ ሰ/ት/ቤት አዳራሽ ተመርቀዋል።

የአባቴ ተረቶች

ሕይወት ቦጋለ

ሐምሌ 16/2003 ዓ.ም.

 
ሌሊቱን ለረጅም ሰዓታት የዘነበው ዝናብ አባርቶ ቦታውን ለንጋት አብሳሪዋ ፀሐይ ከለቀቀ ቆየት ብሏል፡፡
ከመኝታዬ የተነሣሁት አረፋፍጄ ቢሆንም አሁንም የመኝታ ቤቴን መስኮት ከፍቼ አውራ መንገዱን እየቃኘሁ ነው፡፡ ለምን እንደሆነ ባላውቅም ዘወትር ከእንቅልፌ ስነሣ ሰፈራችን ሰላም ለመሆኗ ማረጋገጫዬ የመኝታ ቤቴ መስኮት ናት፡፡
ሁሉም ወደየ ጉዳዩ እንደየ ሐሳቡ መለስ ቀለስ ይለዋል፡፡ የቸኮለ ይሮጣል፣ ቀደም ብሎ የተነሣው ዘና ብሎ ይራመዳል፡፡ ሥራ ፈቱ ይንገላወድበታል ብቻ መንገዱ ለሁሉም ያው መንገድ ነው፡፡ እንደ እኔ ላጤነው ከቁም ነገር ቆጥሮ ላየው ደግሞ ለዓይን ወይም ለአእምሮ የሚሆን አንድ ጉዳይ አይታጣበትም፡፡ ያባቴን ተረቶች ናፋቂ ነኝና ወደሳሎን ወጣሁ፡፡

በወቅታዊ ጉዳዮች ዙሪያ የአዲስ አበባ ሰንበት ት/ቤቶች የአቋም መግለጫ አወጡ።

በተ/ሥላሴ ጸጋ ኪሮስ
ሐምሌ 11፣ 2003 ዓ.ም
የአዲስ አበባ ሰንበት ት/ቤቶች ወቅታዊውን የተሐድሶ መናፍቃንን እንቅስቃሴና ተዛማጅ ጉዳዮችን አስመልክተው መግለጫ አወጡ። በሰ/ት/ቤቶች ማደራጃ መምሪያ ኃላፊ በልዩ ልዩ የመገናኛ ብዙሃን ከመምሪያው ሊቀ ጳጳስ እውቅና ውጭ «ተሐድሶ የሚባል ነገር የለም» በሚል የተሰጠው መግለጫ ሰ/ት/ቤቶች የማይቀበሉት መሆኑን አሳወቁ።