Entries by Mahibere Kidusan

የአዳዲስ ፊዳላት፣ አዳዲስ ቁጥሮች፣ አፈጣጠር ሂደትና አስፈላጊነት

ሚያዚያ 20/2004 ዓ.ም. ሠዓሊ አምሳሉ ገብረ ኪዳን አርጋው ኢትዮጵያ ያሏትን መንፈሳዊና ቁሳዊ የታሪክ ዕሴቶች በማበርከት በኩል የቤተክርስቲያናችን ሊቃውንት ድርሻ ታላቅ መሆኑ ለማንም ግልጽ ነው፡፡ ከእነዚህ ዕሴቶቻችን መካከል ደግሞ በዓለም አቀፍ ደረጃ ስሟን የሚያስጠራና እንደ አፍሪካዊነታችን ብቸኛ ባለቤት እንድንሰኝ የሚያደርጉን ፊደላትና ቁጥሮች ናቸው፡፡ ይህን የሊቃውንቱን አርአያነት ያለው ተግባር ተከትለን የበለጠ ማርቀቅና ሃይማኖት ብቻ ሳይሆን በፍልስፍናና በፈጠራ […]

የጎንደር ደብረ ኀይል ወደብረ ጥበባት በዓታ ለማርያም የአቋቋም ምስክር ትምህርት ቤት ግንባታ ውል ተፈረመ፡፡

ሚያዝያ 18/2004 ዓ.ም.

በእንዳለ ደምስስ

Gedamate 3ማኅበረ ቅዱሳን በሰሜን ጎንደር ሀገረ ስብከት የሚገኘውን የደብረ ኀይል ወደብረ ጥበባት በዓታ ለማርያም የአቋቋም ምስክር ትምህርት ቤትን በ4.6 ሚሊዮን ብር ለመገንባት ሚያዚያ 12 ቀን 2004 ዓ.ም. የግንባታ ውል ስምምነት ከአስማማው አያሌው ሕንጻ ሥራ ተቋራጭ ጋር ተፈራረመ፡፡ በማኅበረ ቅዱሳን የቅዱሳት መካናት ልማትና ማኅበራዊ አገልግሎት ዋና ክፍል አስተባባሪነት የሚከናወነው ይኸው ፕሮጀክት ማኅበረ ቅዱሳንን በመወከል የማኅበሩ ዋና ጸሐፊ ዲ/ን ሙሉጌታ ኀ/ማርያምና የሕንፃ ሥራ ተቋራጩ ባለቤትና ሥራ አስኪያጅ አቶ አስማማው አያሌው አማካይነት የፊርማ መርሐ ግብሩ ተፈጽሟል፡፡

“አብዝቶ የመመገብ ጣጣው”

(በቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ)

ግንቦት 30/2003 ዓ.ም.

ዲ/ን ሽመልስ መርጊያ

መግቢያ

ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ የዮሐንስን ወንጌል በተረጎመበት በ21ኛው ድርሳኑ “ ጌታችን በእናታችን በቅድስት ድንግል ማርያም ጥያቄ በቃና ሰርግ ላይ ስለምን ውሃውን ወደ ወይን ጠጅነት እንደቀየረው  ከአብራራ በኋላ ከዛሬ 1500 ዓመት በፊት በአሁኑ ጊዜ እንደ አዲስ ግኝት ተደርገው የሚታዩትን አብዝቶ በመመገብ የሚመጡትን የጤና ጉድለቶች ጽፎልን እናገኛለን ፡፡ ጽሑፉ ተተርጉሞ እንዲህ ቀርቦአል።


ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ውሃውን ወደ ወይን ጠጅነት ያኔ እንደቀየረ ዛሬም እኛን ድካማችንንና እንደ ወራጅ ውሃ በአንድ ቦታ ጸንቶ መቆየት የተሣነውን የሥጋ ፈቃዳችንን ከመቀየር አልተቆጠበም ፡፡ ዛሬም አዎን ዛሬም ልክ እንደ ወራጅ ውሃ ቀዝቃዛ ፣የፈጠነና ፣ ያልተረጋጋ ጠባይ ያላቸው ሰዎች አሉ ፡፡ እነዚህን ፈቃዶቻችንን ወደ ጌታችን እናምጣቸው ፤ እርሱ ወደ ወይንነት ይቀይራቸዋል፡፡ ከዚያም በኋላ ውኃ ሆነው ከእንግዲህ አይቀጥሉም ፡፡ ነገር ግን ለራሳቸውና ለሌሎች ደስታን የሚሰጡ አካላት ይሆናሉ ፡፡

ማእከሉ የበገና ደርዳሪዎችን አስመረቀ

ማእከሉ የበገና ደርዳሪዎችን አስመረቀ
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ሰንበት ትምህርት ቤቶች ማደራጃ መምሪያ የማኅበረ ቅዱሳን የልማት ተቋማት አስተዳደር የአቡነ ጎርጎርዮስ የአብነትና የዜማ መሣሪያዎች ትምህርትና ሥልጠና ማእከል ለስድስት ወራት በበገና ድርደራ ያሰለጠናቸውን ከ175 በላይ የሚሆኑ የበገና ደርዳሪዎች መጋቢት 29 ቀን 2004 ዓ.ም. በቤተ ክህነት አዳራሽ አስመረቀ፡፡
የትምህርት ማእከሉ ሥራ አስኪያጅ የሆኑት አቶ አብዮት እሸቱ ባደረጉት ንግግር ማእከሉ ሲቋቋም በ1996 ዓ.ም. በ12 ተማሪዎች ትምህርቱን እንደጀመረና በአሁኑ ወቅት በርካታ ተማሪዎችን አቅፎ እያስተማረ እንደሚገኝ፣ በአሳሳቢ ሁኔታ እየቀነሰ የመጣውን የበገና ደርዳሪዎች ቁጥር በመጨመር ረገድ የአባቶቻችንን አሻራ ለተተኪ ትውልድ ለማስተላለፍ ማእከሉ ከፍተኛ ጥረት በማድረግ ላይ መሆኑንና በቀጣይነትም በተለያዩ የሀገሪቱ ክፍሎች ለማስፋፋት እቅድ እንዳለው ገልጸዋል፡፡
የበገና ድርደራ ሥልጠናውን ወስዶ በእለቱ ከተመረቁት ወጣቶት መካከል ወጣት ሔኖክ መንግሥቱ ለስድስት ወራት ትምህርቱን እንደተከታተለና “በመማሬ ብዙ ተጠቅሜያለሁ፤ ሥርዐተ ቤተ ክርስቲያንን የጠበቀ መዝሙር እንዳውቅ አድርጎኛል፡፡ ከዚህም ባለፈ ቤተ ክርስቲያን የምትጠቀምባቸው የዜማ መሣሪያዎች የትኞቹ እንደሆኑ፤ በግል ሕይወቴም ትሕትናንና ትእግስትን በመላበስ በቤተ ክርስቲያን አገልግሎት ጥሩ ሥነ ምግባር እንዲኖረኝ አድርጎኛል” በማለት ገልጿል፡፡
በዕለቱም ብጹዐን ሊቃነ ጳጳሳት፣ ሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያን፣ የተመራቂ ቤተሰቦች ጥሪ የተደረገላቸው ተጋባዥ እንግዶችና የቅዱስ ዳዊት የበገና ቤተሰብ አባላት ተገኝተዋል፡፡
ሚያዝያ 13 ቀን 2004 ዓ.ም.
በእንዳለ ደምስስ

 

 

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ሰንበት ትምህርት ቤቶች ማደራጃ መምሪያ የማኅበረ ቅዱሳን የልማት ተቋማት አስተዳደር የአቡነ ጎርጎርዮስ የአብነትና የዜማ መሣሪያዎች ትምህርትና ሥልጠና ማእከል ለስድስት ወራት በበገና ድርደራ ያሰለጠናቸውን ከ175 በላይ የሚሆኑ የበገና ደርዳሪዎች መጋቢት 29 ቀን 2004 ዓ.ም. በቤተ ክህነት አዳራሽ አስመረቀ፡፡
begana

የቅዱስ ያሬድ ድርሰት በሆነው ምዕራፍ ላይ ጥናታዊ ጽሑፍ ቀረበ

ሚያዝያ 13 ቀን 2004 ዓ.ም.

በእንዳለ ደምስስ

‹‹በቅዱስ ያሬድ የዜማ አስተምህሮ የምዕራፍ ሚናና አጠቃቀም›› በሚል ርዕስ ጥናታዊ ጽሑፍ ቀረበ፡፡ በማኅበረ ቅዱሳን ጥናትና ምርምር ማዕከል አስተባባሪነት በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የሥርዓተ ትምህርትና የመምህራን ሙያ ልማት ትምህርት ክፍል ረዳት ፕሮፌሰርና የያሬድ ሙዚቃ ትምህርት ቤት መምህር  በሆኑት ዶክተር ውቤ ካሣዬ አማካይነት በኢትዮጵያ ብሔራዊ ሙዚየም ትልቁ አዳራሽ ቅዳሜ መጋቢት 29/2004 ዓ.ም. ቀርቧል፡፡ የጥናቱ አላማ ስለ ምዕራፍ ጠቀሜታና ክፍሎች መጠነኛ ትንታኔ መስጠት፤ ቅኝት ማድረግ፤ የቅዱስ ያሬድ የዜማ ስልቶችን ታዳሚው ግንዛቤ እንዲኖረው ማድረግና ወደፊት ሊሻሻሉ የሚገባቸው ጉዳዮች ላይ ሃሳብ ማቅረብ እንደሆነ ገልጸው፤ ነገር ግን ጥናቱ ብዙ የሚቀረው ነገር እንዳለው ጨምረው ተናግረዋል፡፡

 

የትንሣኤው ትርጉም በዓሉና አከባበሩ

ከሊቀ ትጉሃን ኀ/ጊዮርጊስ ዳኘ
በጠ/ቤተ ክህነት የዕቅድና ልማት መምሪያ ምክ/ሓላፊ

  • «ትንሣኤ» የሚለው ቃል የግእዝ ቋንቋ ነው፡፡

  •  መገኛ ቃሉም «ተንሥአ» = ተነሣ የሚለው ግሥ ይሆናል፡፡

  • «ትንሣኤ» ማለት ታዲያ = መነሣት፣ አነሣሥ ሐዲስ ሕይወት ማግኘት ማለትን ያመለክታል፡፡

  •  «ትንሣኤ» በሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያን በየመልኩ፣ በየዐይነቱ ሲተረጐም ዐምስት ክፍል አለው፡፡

  • «ትንሣኤ» የሚለው ቃል የግእዝ ቋንቋ ነው፡፡

  • መገኛ ቃሉም «ተንሥአ» = ተነሣ የሚለው ግሥ ይሆናል፡፡

  • «ትንሣኤ» ማለት ታዲያ = መነሣት፣ አነሣሥ ሐዲስ ሕይወት ማግኘት ማለትን ያመለክታል፡፡

  • «ትንሣኤ» በሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያን በየመልኩ፣ በየዐይነቱ ሲተረጐም ዐምስት ክፍል አለው፡፡

ዳግም ትንሣኤ (ለሕፃናት)

ሚያዝያ 12/2004 ዓ.ም.

በእኅተ ፍሬስብሐት

st.Tomasጌታችን በተነሣበት ዕለት የክርስቶስ ደቀመዛሙርት ተሰብስበው ሳለ ጌታችን በመካከላቸው ቆመና “ሰላም ለእናንተ ይሁን “አላቸው፡፡ የነበሩበት ቤት በሩም መስኮቱም ተቆልፎ ስለነበር ደቀ መዛሙርቱም በጣም ደነገጡ፡፡ ጌታችን መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስም  “አትፍሩ እኔ አምላካችሁ ነኝ” ብሎ የተወጋ ጎኑን እና የተቸነከሩ እጆቹን አሳያቸው፡፡ እነርሱም ጌታ ከሞት መነሣቱን አመኑ፡፡ ደቀመዛሙርቱንም(ተማሪዎቹንም) ሕዝቡን እንዲያስተምሩ ላካቸው፡፡

“ክርስቶስ ተንሥአ እሙታን፤ በዐቢይ ኃይል ወሥልጣን፤ አሰሮ ለሰይጣን፤ አግዐዞ ለአዳም፤ ሠላም እምይዕዜሰ፤ ኮነ፤ ፍስሐ ወሠላም፡፡”

በመ/ር ምሥጢረ ሥላሴ ማናየ

“ክርስቶስ በታላቅ ኃይልና ሥልጣን ከሙታን ተለይቶ ተነሣ ዲያብሎስን አሰረው አዳምን ነጻ አወጣው ሠላም ከዛሬ ጀምሮ ሰላም ሆነ” ይህ ቃል የትንሣኤው የምሥራች ለምእመናን የሚታወቅበት ነው የሚቀድስ ካህን፣ ሰባኪ በዘመነ ትንሣኤ ከስብከቱ አስቀድሞ በዚህ ቃል የክርስቶስን መነሣት ያውጃል፡፡ የሚቀድሰው ካህንም በኪዳን ጊዜ ህዝቡን ከመባረኩ አስቀድሞ ይህንኑ ቃል ይናገራል ሰላምታ የሚቀባበሉ ምእመናንም ሰላምታ ከመስጠት አስቀድሞ ይህን ቃል በመናገር የትንሣኤውን አዋጅ ማወጅና መመስከር ይገባቸዋል፡፡ እንኳን ለብርሃነ ትንሣኤው አደረሰን አደረሳችሁ፡፡

ቀዳም ሥዑር

ሚያዝያ 6፣2004 ዓ.ም.

ቅዳሜ፡

ቀዳም ሥዑር ይባላል፡፡ በዚች ዕለች ከድሮው በተለየ መልኩ የጌታችንን መከራ በማሰብ በጾም ታስባ ስለምትውል የተሻረችው ቅዳሜ ትባላለች፡፡

የማትጾመዋ ቅዳሜ ስለምትጾም ስዑር /የተሻረች/ ተብላለች በዓል መሻርን አይመለከትም በቀዳም ሥዑር  ሌሊት ሥርዓቱ የሚጀመረው በመኀልየ ሰሎሞን ምንባብ ነው፡፡ ማኀሌቱም እዝሉ እየተቃኘ እየተመጠነ፣ እየተዘመመ እየተመረገደ እየተጸፋ ያድራል፡፡ ጥዋት አቡን መዋሥዕት ውዳሴ ማርያም ዜማ ተደርሶ ወለመልአከ ሕይወትሰ ሰቀልዎ በሚለው ሰላም ይጠናቀቃል፡፡በዚህ ዕለት ልብሰ ተክህኖ የለበሱ ካህናትና ዲያቆናት ቄጤማ ተሸክመው ቃጭል ሲያቃጨሉ መታየታቸው ዕለተ ትንሣኤውን ለሚናፍቅ ምእመን ትልቅ ብስራት ነው፡፡