begana

ማእከሉ የበገና ደርዳሪዎችን አስመረቀ

ማእከሉ የበገና ደርዳሪዎችን አስመረቀ
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ሰንበት ትምህርት ቤቶች ማደራጃ መምሪያ የማኅበረ ቅዱሳን የልማት ተቋማት አስተዳደር የአቡነ ጎርጎርዮስ የአብነትና የዜማ መሣሪያዎች ትምህርትና ሥልጠና ማእከል ለስድስት ወራት በበገና ድርደራ ያሰለጠናቸውን ከ175 በላይ የሚሆኑ የበገና ደርዳሪዎች መጋቢት 29 ቀን 2004 ዓ.ም. በቤተ ክህነት አዳራሽ አስመረቀ፡፡
የትምህርት ማእከሉ ሥራ አስኪያጅ የሆኑት አቶ አብዮት እሸቱ ባደረጉት ንግግር ማእከሉ ሲቋቋም በ1996 ዓ.ም. በ12 ተማሪዎች ትምህርቱን እንደጀመረና በአሁኑ ወቅት በርካታ ተማሪዎችን አቅፎ እያስተማረ እንደሚገኝ፣ በአሳሳቢ ሁኔታ እየቀነሰ የመጣውን የበገና ደርዳሪዎች ቁጥር በመጨመር ረገድ የአባቶቻችንን አሻራ ለተተኪ ትውልድ ለማስተላለፍ ማእከሉ ከፍተኛ ጥረት በማድረግ ላይ መሆኑንና በቀጣይነትም በተለያዩ የሀገሪቱ ክፍሎች ለማስፋፋት እቅድ እንዳለው ገልጸዋል፡፡
የበገና ድርደራ ሥልጠናውን ወስዶ በእለቱ ከተመረቁት ወጣቶት መካከል ወጣት ሔኖክ መንግሥቱ ለስድስት ወራት ትምህርቱን እንደተከታተለና “በመማሬ ብዙ ተጠቅሜያለሁ፤ ሥርዐተ ቤተ ክርስቲያንን የጠበቀ መዝሙር እንዳውቅ አድርጎኛል፡፡ ከዚህም ባለፈ ቤተ ክርስቲያን የምትጠቀምባቸው የዜማ መሣሪያዎች የትኞቹ እንደሆኑ፤ በግል ሕይወቴም ትሕትናንና ትእግስትን በመላበስ በቤተ ክርስቲያን አገልግሎት ጥሩ ሥነ ምግባር እንዲኖረኝ አድርጎኛል” በማለት ገልጿል፡፡
በዕለቱም ብጹዐን ሊቃነ ጳጳሳት፣ ሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያን፣ የተመራቂ ቤተሰቦች ጥሪ የተደረገላቸው ተጋባዥ እንግዶችና የቅዱስ ዳዊት የበገና ቤተሰብ አባላት ተገኝተዋል፡፡
ሚያዝያ 13 ቀን 2004 ዓ.ም.
በእንዳለ ደምስስ

 

 

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ሰንበት ትምህርት ቤቶች ማደራጃ መምሪያ የማኅበረ ቅዱሳን የልማት ተቋማት አስተዳደር የአቡነ ጎርጎርዮስ የአብነትና የዜማ መሣሪያዎች ትምህርትና ሥልጠና ማእከል ለስድስት ወራት በበገና ድርደራ ያሰለጠናቸውን ከ175 በላይ የሚሆኑ የበገና ደርዳሪዎች መጋቢት 29 ቀን 2004 ዓ.ም. በቤተ ክህነት አዳራሽ አስመረቀ፡፡
begana
የበገና ድርደራ ሥልጠናውን ወስዶ በእለቱ ከተመረቁት ወጣቶት መካከል ወጣት ሔኖክ መንግሥቱ ለስድስት ወራት ትምህርቱን እንደተከታተለና “በመማሬ ብዙ ተጠቅሜያለሁ፤ ሥርዐተ ቤተ ክርስቲያንን የጠበቀ መዝሙር እንዳውቅ አድርጎኛል፡፡ ከዚህም ባለፈ ቤተ ክርስቲያን የምትጠቀምባቸው የዜማ መሣሪያዎች የትኞቹ እንደሆኑ፤ በግል ሕይወቴም ትሕትናንና ትእግስትን በመላበስ በቤተ ክርስቲያን አገልግሎት ጥሩ ሥነ ምግባር እንዲኖረኝ አድርጎኛል” በማለት ገልጿል፡፡

 

የትምህርት ማእከሉ ሥራ አስኪያጅ የሆኑት አቶ አብዮት እሸቱ ባደረጉት ንግግር ማእከሉ ሲቋቋም በ1996 ዓ.ም. በ12 ተማሪዎች ትምህርቱን እንደጀመረና በአሁኑ ወቅት በርካታ ተማሪዎችን አቅፎ እያስተማረ እንደሚገኝ፣ በአሳሳቢ ሁኔታ እየቀነሰ የመጣውን የበገና ደርዳሪዎች ቁጥር በመጨመር ረገድ የአባቶቻችንን አሻራ ለተተኪ ትውልድ ለማስተላለፍ ማእከሉ ከፍተኛ ጥረት በማድረግ ላይ መሆኑንና በቀጣይነትም በተለያዩ የሀገሪቱ ክፍሎች ለማስፋፋት እቅድ እንዳለው ገልጸዋል፡፡

begena graduate

በዕለቱም ብጹዐን ሊቃነ ጳጳሳት፣ ሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያን፣ የተመራቂ ቤተሰቦች ጥሪ የተደረገላቸው ተጋባዥ እንግዶችና የቅዱስ ዳዊት የበገና ቤተሰብ አባላት ተገኝተዋል፡፡