ወርኃ ታኅሣሥ
ሰፊ አስተምህሮ እና ምሥጢር ካላቸው ወራት አንዱ የታኅሣሥ ወር ነው። በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ አስተምህሮ በባሕረ ሐሳብ ቀመር ቀኑ ዘጠኝ ሌሊቱ ዐሥራ አምስት ይሆናል፤ ከዚህ በኋላ ቀኑ እየጨመረ ሌሊቱ እያነስ ይሄዳል
This author has not written his bio yet.
But we are proud to say that Mahibere Kidusan contributed 975 entries already.
ሰፊ አስተምህሮ እና ምሥጢር ካላቸው ወራት አንዱ የታኅሣሥ ወር ነው። በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ አስተምህሮ በባሕረ ሐሳብ ቀመር ቀኑ ዘጠኝ ሌሊቱ ዐሥራ አምስት ይሆናል፤ ከዚህ በኋላ ቀኑ እየጨመረ ሌሊቱ እያነስ ይሄዳል
ውድ የእግዚአብሔር ልጆች! እንዴት አላችሁልን? እንኳን ለጾመ ነቢያት (ለገና ጾም) አደረሳችሁ! ጾመ ነቢያት አባቶቻችን ነቢያት አምላካችን ተወልዶ ያድነን ዘንድ የጾሙት ጾም ነው፤ እኛ ደግሞ ከሰማያት ወርዶ፣ ከእመቤታችን ከቅድስት ድንግል ማርያም ተወልዶ አድኖናል ስንል ውለታውንና ፍቅሩን እያሰብን እንጾማለን!
በዘመናዊ ትምህርታችሁ የዓመቱን አንድ አራተኛ (ሩቡን የትምህርት ዘመን) ጨረሳችሁ አይደል! መቼም ከነበራችሁ ዕውቀት እንደጨመራችሁ ተስፋ እናደርጋለን! በርትታችሁ ተማሩ እሺ! መልካም!
ባለፈው ተከታታይ ትምህርታችን ስለ አማላጅነት ምንነት፣ ስለ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም እና ስለ ቅዱሳን መላእክት አማላጅነት በተወሰነ መልኩ ተምረን ነበር፤ ዛሬ ደግሞ ስለ ቅዱሳን አባቶቻችንና እናቶቻችንን አማላጅነት እንማራለን! ተከታተሉን!
ምድር ዛሬ እያለቀሰች ነው፡፡ ግን እስከ መቼ ታለቅሳለች? ሰዎችስ ከክፋታቸው የሚመለሱት መቼ ነው? የምድረ በዳው ሣርስ እስከ መቼ ደርቆ ይቀጥላል? አዕዋፋትና እንስሳትስ እስከ መቼ ያልቃሉ? እግዚአብሔርስ ምድርን እስከ መቼ ነው የሚቆጣት? ቅዱሳንስ ስለ ደማቸው እስከ መቼ ምድርን ይካሰሷታል? ነቢዩ ኤርምያስ የሚጠይቀውን ጥያቄ አሁንም እኛ እንጠይቃለን፡፡
በኤርምያስ ዘመን የሆነው እንዲህ ነበር፡፡ ልክ እንደ ዛሬው ክፉዎች ሠልጥነው ነበር፤ ከመከራቸው የተነሣ ልጆች፣ ድሃ አደጎችና አባት እናት የሌላቸው ሕፃናት ብዙዎች ነበሩ፤ እናቶች እንደ መበለቶች ሆነው ነበር፡፡ ውኃቸውን በብር እንጨቶቻቸውን፣ በዋጋ ገዝተው የተጠቀሙበት ጊዜ ነበር፡፡
የገባልሽ ኪዳን የሰጠሽ መሐላ
ከንቱ ነበረ ወይ የጨረቃ ጥላ?
በአጋንንት ፍላጻ ነፍሴ ብትወጋ
ምልጃሽ ነው ተስፋዬ ከጥላሽ ልጠጋ፡፡
ጽዮን ሆይ ክበቢኝ ለውዳሴሽ ልትጋ
የኃጢአት ጎዳናዬ መንገዴ ይዘጋ!
ሐመረ ብርሃን የብራና መጻሕፍት ሥራ ድርጅት በኅዳር ፲፭፤ ፳፻፲፯ ዓ.ም. በጠቅላይ ቤተ ክህነት በአካሄደው የምስጋና መርሐ ግብር ላይ የተገኙት የጠቅላይ ቤተ ክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ እና የባሕር ዳርና ሰሜን ጎጃም ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ አብርሃም ባስተላለፉት መልእክት የብራና መጽሐፍት ዝግጅት ረጅም ጊዜ የሚወስድ በመሆኑ እየተዳከመ የመጣ ቢሆንም ዛሬ ላይ በዚህ መልክ እያደገ መምጣቱ የሚያስደስት መሆኑን አክለው ገልጸዋል፡፡
ይህ ሱባኤ፣ ዘመነ ነቢያት፣ ወርኃ ጾመ ነቢያት ከመቼውም በላይ አስጨናቂዎቻችን፣ በሥጋ በነፍስ የሚዋጉን፣ አጋንንት ውሉደ አጋንንት፣ ረቂቃኑ አጋንንት፣ ልቡሰ ሥጋ አጋንንት፣ ሁሉ እንደ ጤዛ ረግፈው፣ እንደ ትቢያ ተበትነው፣ ከሕዝበ ክርስቲያንና ከቤተ ክርስቲያን ይርቁ ዘንድ፣ የክርስቶስም መንጋ በሰላም በበረቱ ያድር ዘንድ፣ ‹‹እጅህን ከአርያም ላክ፤ አድነንም›› የምንልበት ጊዜ ነው፡፡
ውድ የእግዚአብሔር ልጆች! ለከበረው ጤንነታችሁ እንዴት አላችሁልን?! በፈቃደ እግዚአብሔር አዲሱን ዓመት ከተቀበልን ሁለት ወራትን አሳልፈን ሦስተኛውን ጀምረናል! ለዚህ ያደረሰን አምላክ ይመስገን! ለመሆኑ ትናንት ከነበረው ማንነታችሁ ላይ ምን ለውጥ አመጣችሁ? በዘመናዊ ትምህርትስ ምን ያህል ዕውቀትን ሸመታችሁ? በመንፈሳዊ ሕይወታችሁስ በሥነ ምግባር ምን ያህል ለውጥ አመጠችሁ? በርትታችሁ መማር ይገባል፤
….ባለፈው ተከታታይ ትምህርታችን ስለ አማላጅነት ትርጉም እንዲሁም ስለ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም አማላጅነት ተምረን ነበር፡፡ በዚህ የትምህርት ክፍለ ጊዜያችን ደግሞ ስለ ቅዱሳን መላእክት አማላጅነት እንማራለን! መልካም!
የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ሃይማኖታዊ ነጻነታቸውን የሚጋፋ መመሪያ መውጣቱን ገለጹ፡፡ ዮኒቨርስቲው በ፳፻፲፯ ዓ.ም ያወጣውን የሥነ ምግባርና ዲሲፕሊን መመሪያ ተከትሎ ይህንን መመሪያ ማውጣቱን ተማሪዎቹ አክለው ገልጸዋል፡፡
እኔም ልመለስ ድንግል እናቴ
ከስደት ሕይወት ከባርነቴ
በልጅሽ ጉንጮች በወረደ ዕንባ
ባዘነው ልብሽ በተላበሰው የኀዘን ካባ
በእናት አንጀትሽ እንስፍስፍ ብሎ ያኔ በባባ
ልመለስ ድንግል ሆይ እኔም ከስደት
እውነትን ልያዝ ልራቅ ከሐሰት፡፡
ጥላቻ ገዝቶኝ ወንድሜን ከጠላው
እምነት ምግባሬን ሰይጣን ዘረፈው
መልሽኝ ድንግል ይብቃኝ ግዞቱ
በምግባር እጦት በቁም መሞቱ!