Entries by Mahibere Kidusan

ጾመ ሰብአ ነነዌ

‹‹ጾመ ሰብአ ነነዌ፤ የነነዌ ሰዎች ጾም›› የሦስት ቀን ጾም የጾሙት በነነዌ ይኖሩ የነበሩ ሰዎች ናቸው፡፡ ከተማዋም (ነነዌ) በጤግሮስ ወንዝ ዳርቻ የምትገኝ ስትኾን መሥራቿም ናምሩድ ነው (ዘፍ.፲፥፲፩-፲፪)፡፡ ጥንታዊቷ የነነዌ ከተማ ለአሦር መነሻ የሆነች፤ እጅግ ሰፊና ያማረች፤ የቅጥሯ ርዝመትም ፲፪ ኪሎ ሜትር የሚሸፈን ነበር፡፡ በከተማዋ ንጉሡ ሰናክሬም ብዙ ሕንጻዎችን ገንብቶ ነበር (ዮናስ ፬፥፲፩)፡፡

የኢትዮጵያውያን ቅዱሳት አንስት አርአያነት

የቅዱሳት አንስት ገድል እንደ አርአያና ምሳሌ ሆኖ ለብዙ ምእመናን ትምህርት ሊሆን የሚችል ታሪክ ነው። የእነዚህም አንስት ተጋድሎ እንደየዘመናቱ ቢለያይም ለሕዝቡ ካለው ሚና አንጻር ሁሌም አስፈላጊነቱ የላቀ ነው፡፡

ሥርዓተ ንባብ

ውድ አንባብያን በአለፈው ትምህርታችን ከምንባቡ ላይ ተነሽ ንባባትን እንድትጽፉ መልመጃ መስጠታችን ይታወቃል። እንደሠራችሁትም ተስፋ እናደርጋለን። ለማረጋገጥ ያህል ምንባቡንና መልሱን እንደሚከተለው እናቀርባለን።

‹‹ጊዜ ዕረፍታ ለሶልያና››

እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም በምድር ላይ በአይሁድ ክፋት ብዙ መከራና ኃዘንን ካሳለፈች በኋላ በዘመነ ሉቃስ ጥር ሃያ አንድ ቀን በስድሳ አራት ዓመቷ ወደ ዘለዓለም ደስታ ትገባ ዘንድ ዐርፋለች፡፡

ጸሎትና ክርስቲያናዊ ሕይወት

ጸሎት ክርስቲያኖች ከሚያከናውኗቸው መንፈሳዊ ተግባራት ውስጥ አንዱ ነው፡፡ ክርስቲያን በጸሎት የሚተጋ ሰው ነው፤ ያለ ምግብ ሰው መኖር እንደማይችል ሁሉ ክርስቲያንም ያለ ጸሎት መኖር አይችልም፡፡ ከውኃ ውስጥ የወጣ ዓሣ ሕይወት እንደማይኖረው ሁሉ ከጾም ከጸሎት እና ከንስሓ ሕይወትም የተለየ ክርስቲያን የሞተ ነው፤ ሕይወት የሌለው በነፋስ ብቻ የሚንቀሳቀስ በድንም ይሆናል፤ መጸለይ ሕይወት ነውና፤ አለመጸለይ ደግሞ የነፍስ ሞት ነው፡፡

ሰማዕታት ቅድስት ኢየሉጣ እና ሕፃን ቂርቆስ

ቅድስት ኢየሉጣ በሮም ግዛት በሚገኝ አንጌቤን በሚባል አገር በፈሪሃ እግዚአብሔር፣ በክርስትና ሃይማኖት እና በበጎ ምግባር ጸንታ ትኖር የነበረች ደግ ሴት ነበርች፡፡ በሥርዓት ያሳደገችው ቂርቆስ የሚባል ሕፃን ልጅም ነበራት፡፡

‹‹ከዚህም በረት ያልሆኑ ሌሎች በጎች አሉኝ፤ እነርሱን ደግሞ ላመጣ ይገባኛል፤ ድምጼንም ይሰማሉ፥ አንድ መንጋም ይሆናሉ እረኛውም አንድ ነው›› (ዮሐ. ፲፥ ፲፮)

ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በአንቀጸ አባግዕ ሲያስተምር ‹‹ከዚህም በረት ያልሆኑ ሌሎች በጎች አሉኝ፤ እነርሱን ደግሞ ላመጣ ይገባኛል፤ ድምጼንም ይሰማሉ፥ አንድ መንጋም ይሆናሉ እረኛውም አንድ ነው›› ብሏል።(ዮሐ. ፲፥ ፲፮)

ጥምቀተ ክርስቶስ

በቅዱስ ዮሐንስ እጅ በማየ ዮርዳኖስ ተጠምቆ የባሕርይ ልጅነቱንና አምላክነቱን ከአብ እና ከመንፈሰ ቅዱስ አስመሰከረ፡፡

ዘመነ አስተርእዮ

አስተርእዮ መታየት ወይም መገለጥ የሚል ትርጓሜ ያለው የግእዝ ቃል ነው፡፡ በግሪክ ‹‹ኤጲፋኒ›› የሚል ስያሜ አለው፤ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ሊቃውንትም ይህን ቃል በመጠቀም ኤጲፋኒያ እያሉ በዜማ መጻሕፍቶቻቸው ይጠሩታል፡፡